ኦባማ የሚባል መንፈስ (ፕ/ር መስፍን ወ/ማርያም)

መስፍን ወልደማርያም (ፕ/ር) ጥር 2000

Prof. Mesfin Woldemariamአሜሪካ ጉድ ፈልቶበታል! አሜሪካ በነቡሹም ቢሆን የታወቀ የነፃነት አገር ነው፤ ይህንን እውነት ሊክዱ የሚዳዳቸው ሰዎች በተለይም አምባ-ገነኖች ሞልተዋል። ነጻነት መንታ መልኮችና ባሕርዮች አሉት፤ በአንድ በኩል በጎና ሰላማዊ፣ ሥራንና ሀብትን ፈጣሪ ሲሆን፣ በሌላ በኩል ደግሞ እኩይና ቀጣፊ፣ የሌላውን ሀብት ዘራፊና የወንጀል ፈልፋይ ይሆናል። የነጻነት ባሕርይ ያልገባቸውና ነጻነትን የሚፈሩት እኩዩን የነጻነት ባሕርይ ለማፈን ሲሉ በጎውንም ባሕርዩን አብረው ይከረችሙታል። ምድረ አሜሪካ ሁለቱም የነጻነት ባሕርዮች በገሀድ የሚታዩበት ነው። በአሜሪካ ጉልበትና ገንዘብ ማናቸውንም ነገር የሚያነቃንቁ ኃይሎች ናቸው። እነዚህ ኃይሎች ሕጉን ቢያዶለዱሙትም በትክክል ይሠራል። ጉልበትና ገንዘብ ያላቸው ሁሉ የልማት እንቅስቃሴውን ብቻ ሳይሆን የዜና ማሰራጫዎቹን ሁሉ በቁጥጥራቸው ስር አድርገው የፈለጉትን ፖለቲከኛ የሚያነሡትና ወይም የሚጥሉት እነሱ ናቸው። 

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ስዬ አብርሃ - አዲስ ወይን ጠጅ ባዲስ አቁማዳ ወይስ አሮጌ ወይን ጠጅ ባዲስ አቁማዳ? (ተስፋሚካኤል)

ተስፋሚካኤል ሳህለስላሴ - ካናዳ

እንደማስጠንቀቂያ፡- እንድታውቁት ያህል

አቶ ስዬ አብርሃ በፈረንጆቹ አዲስ ዓመት መግቢያ ላይ በዋሽንግተን አካባቢ ያደረጉትን ውይይት ለመካፈል ስሄድ፣ ማንም የሚረዳውና የሚገምተው ጥርጣሬና ጥያቄ በውስጤ ቋጥሬ ነበር። መቼም እኚህን መከራችንን ካመጡትና ካበዙት አንዱ የሆኑትን ሰው ለማየትና ለመስማት ስሄድ፤ የምደግፋቸውና የምከተላቸው ዶ/ር ያዕቆብ ወይም ብርቱካን ሲመጡ እየዘለልኩና በሙሉ ልብ፣ እንዲሁም በመተማመን እንደተቀበልኳቸው አቶ ስዬንም ገና ለገና ከኢህአዴግ ስለተጣሉ ብቻ ያለምንም ጥያቄ እንድቀበል የሚጠብቅ ያለ አይመስልኝም። ‘አብዮት ልጇን ትበላለች’ የሚለው አባባል የቅርብ ግዜ የሕይወት ማስረጃ የሆኑትን አቶ ስዬ ቀርቶ፣ እነዚያ ስናጨበጭብላቸውና ስናቆላምጣቸው የኖርነው የቅንጅት መሪዎችም ሲመጡ አንዳንዶች በምን መልኩ እንደተቀበሏቸው ያስተዋለ፤ አቶ ስዬ ላይ በሚነሱ ጥርጣሬዎችና ተቃውሞዎች ሊደነግጥም ሊበሳጭም አይገባም።

ሙሉውን አስነብበኝ ...