ምስጢሩ - ፩

The Secret ምስጢሩወለላዬ ከስዊድን
"The Secret" በሚል ርዕስ አውስትራሊያዊቷ ሮዳ ቢየርን ጽፋው፣ ጋሻው አባተ "ምስጢሩ" በማለት ወደ አማርኛ የመለሰውን መጽሐፍ በአድናቆት አነበብኩ። ምስጢሩ ... "ወዳንተ የሚመጣውን ማንኛውንም ነገር ወደ ሕይወትህ የምትጎትተው አንተው ነህ" ይለናል። አዎን! በእርግጥ ብዙዎች ምስክርነት ሰጥተውበታል። ይህም በመጽሐፉ ላይ ተካቶ ይገኛል። መጽሐፉ በአስራ አንድ ርዕሶች የተከፋፈለ ነው። ከዛ ውስጥ የመጀመሪያውን ዕርስ ማጠቃለያ ፍሬ ሀሳብ፤ በግጥም ስሠራው እንዲህ እንሶና ጭምቅ ብሎ ወጣልኝ። ለወገኖቼ ባካፍልስ ብዬ አሰብኩ፤ ወደናንተም ላኩት። ሁለተኛው ርዕስና ሌሎቹም ይቀጥላሉ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ከ"ድርጅታዊ ምዝበራ" መጽሐፍ ላይ የተወሰደ ማስታወሻ

"ድርጅታዊ ምዝበራ" በዶ/ር አክሎግ ቢራራገለታው ዘለቀ

በቅርቡ ለንባብ የበቃው "ድርጅታዊ ምዝበራ" የተሰኘው መጽሐፍ ደራሲ ዶክተር አክሎግ ቢራራ ጎንደር ተማሪ በነበሩበት ወቅት በአንድ ነገር ተመስጠው ነበር። ይህ ምናባቸውን የገዛው ነገር በጎንደር ውስጥ እድሜው የትየለሌ የሆነ የአንድ የዋርካ ዛፍ ተፈጥሮ ነበር።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የዶ/ር ምህረት ደበበ “የተቆለፈበት ቁልፍ”

Yetekolefebet qulfብርሃኑ ሰሙ

ከሁለት ወር በፊት መጋቢት ላይ ነበር “የተቆለፈበት ቁልፍ” የተሰኘው የዶ/ር ምህረት ደበበ ገ/ጻዲቅ ረዥም ልቦለድ መጽሐፍ አንባቢያን እጅ የገባው። መቼቱን በአገር ውስጥና በባህር ማዶ ያደረገው ልቦለድ፤ በ439 ገፆች የተቀነበበ ሲሆን ደራሲው የአእምሮ ህክምና ስፔሺያሊስትነት ደረጃ የደረሱት ትምህርታቸውን በአገር ውስጥ በባሕር ማዶ በመከታተል ነው። በአሁኑ ጊዜ በአሜሪካንና በኢትዮጵያ እየተመላለሱ በሙያቸዉ እያገለገሉ እንደሆነ በመጽሐፋቸው ላይ ተጠቁሟል። ዶ/ር ምህረት፤ ከሐኪምነታቸዉ በተጨማሪ በአስተሳሰብና በአእምሮ ለውጥ ዙሪያ እያስተማሩና ጥናት እየሰሩ እንደሆነ የሚጠቅሰው መረጃው፤ ህብረተሰባዊ ለውጥ ከግለሰቦች የአስተሳሰብ ለውጥ እንደሚጀምር የሚያምኑ መሆናቸውን ይገልፃል። ልቦለድ መጽሐፋቸውም ይሄንኑ የሚያንፀባርቅ ነው። ልቦለዱ በፍቅርና ጥላቻ፣ በደግነትና ክፋት፣ በግልጽነትና መሰሪነት፣ በሀብትና ድህነት፣ በትጋትና ስንፍና፣ በእውቀትና መሃይምነት ዙሪያ የሚያጠነጥን ሲሆን በጠንካራ የልብ ሰቀላ የአንባቢውን ስሜት ይዞ ከመነሻ እስከ መድረሻ ይዘልቃል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ዶ/ር አበራ ጀምበሬ ትዝታዬና መጽሐፉ

ዶ/ር አበራ ጀምበሬ
ዶ/ር አበራ ጀምበሬ

ከመዝገብ ቤት ሠራተኛነት እስከ ሚንስትሮች ምክር ቤት ዋና ጸሐፊነት

ወለላዬ (ከስዊድን)

ዛሬ ብቻ ኖረው - በዛሬ ያልቀሩ

ነገንም አስበው - ለነገ የሠሩ
ለራሳቸው ሳይሆን - ለህዝብ የኖሩ
ግዴታ ሆነና ሞት - ቢሆን ዕጣቸው
ሲበራ ይኖራል - አይጠፋም ሐቃቸው

ግጥም - አስራት ዳምጠው

በስድስተኛ ዓመቴ መጨረሻ ግድም አንድ ቀይ እንግዳ እቤታችን መጣ። ከናትና አባቴ ጋር ሆኜ ከሰውየው ጋር የመቀመጥ እድል አገኘሁ። ቀዩ ሰውዬ ሳቂታ ፊት፣ የሚቁለጨለጩ አይኖች፣ ሰልካካ አፍንጫና፣ የሞሉ ጉንጮች አሉት።ያም ሆኖ ሙሉ ፊቱ ስትታይ አነስተኛ ነች።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የክሽፈት እንጉርጉሮ፣ ታሪክ ላይ ተሸንቅሮ!

መክሸፍ እንደኢትዮጵያ ታሪክካሣሁን ዓለሙ

"አንድ ሰው በአደባባይ ሲናገርም ሆነ ጽሑፍ አሳትሞ ሲያሰራጭ ራሱን አጋልጦአል፤ የተናገረው ወይም የጻፈው መቶ በመቶ ያህል በራሱ ጉዳይ ላይ ብቻ ከሆነ፣ የመተቸት ወይም ሐሳብ የመስጠት ግደታ የለብንም፤ ነገር ግን የተናገረው ወይም የጻፈው በአገርና በሕዝብ ጉዳይ ላይ ከሆነ፣ የዚያ አገር ዜጋ ሁሉ በጉዳዩ ውስጥ የመሳተፍና ሐሳቡን በሙሉ ነጻነት የመስጠት መብት አለው።"

(ፕ/ር መስፍን ወልደማሪያም፣ መክሸፍ እንደኢትዮጵያ ታሪክ፣ ገጽ78-79)

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ