በአርቲስት ሐጫሉ ግድያ ተጠርጥረው የተያዙ ሦስት ሰዎች ፍርድ ቤት ቀረቡ
ከተጠርጣሪዎቹ አንዷ ሴት ነች
ኢዛ (ሐሙስ ሰኔ ፳፭ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. July 2, 2020)፦ በአርቲስት ሐጫሉ ሁንዴሳ ግድያ ተጠርጥረው የተያዙት ሦስት ሰዎች ዛሬ ሐሙስ ሰኔ 25 ቀን 2012 ዓ.ም. ፍርድ ቤት የቀረቡ ሲሆን፣ ከተጠርጣሪዎቹ አንዷ ሴት ነች።
ፖሊስ በእነዚሁ ሁለት ወንዶችና አንድ ሴት ተጠርጣሪዎች ላይ የ14 ቀን የጊዜ ቀጠሮ የጠየቀባቸው ሲሆን፣ ፍርድ ቤቱም ለፖሊስ ጥያቄ አዎንታዊ ምላሽ መስጠቱ ታውቁል።
አርቲስት ሐጫሉ በተገደለ ማግሥት ማክሰኞ ሰኔ 23 ቀን የፌዴራሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጄኔራል እንዳሻው ጣሰው በሰጡት መግለጫ፤ አርቲስቱ መኪናው አቁሞ ወርዶ እንደነበርና፤ ተመልሶ ወደ መኪናው ከገባ በኋላ ተጠርጣሪዎቹ የመኪናውን በር በመክፈት በጥይት እንደመቱት ገልጸዋል። (ኢዛ)