President Isaias Afwerki and Sudan's President of Sovereign Council, LT-General, Abdul Fattah Al-Burhan

የሱዳን የሽግግር መንግሥት ሉዓላዊ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሌተናል ጄኔራል አብዱል ፈታህ አል ቡርሃን ፕሬዝዳንት ኢሳይያስ አፈወርቂን ካርቱም ላይ አቀባበል ሲያደርጉላቸው

የኤርትራን እና የሱዳንን የሁለትዮሽ ትብብሮችን ማጠናከር በሚቻልባቸው ላይ ይመክራሉ

ኢዛ (ሐሙስ ሰኔ ፲፰ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. June 25, 2020)፦ የኤርትራ ፕሬዝዳንት ኢሳይያስ አፈወርቂ የሥራ ጉብኝት ለማድረግ ዛሬ ሐሙስ ሰኔ 18 ቀን 2012 ዓ.ም. ካርቱም ገብተዋል።

ፕሬዝዳንት ኢሳይያስ ጉብኝቱን የሚያደርጉት በሱዳን የሽግግር መንግሥት ሉዓላዊ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሌተናል ጄኔራል አብዱል ፈታህ አል ቡርሃን በቀረበላቸው ግብዣ መሠረት ሲሆን፤ በካርቱም የሦስት ቀናት ቆይታ ይኖራቸዋል ተብሏል።

ፕሬዚዳንቱ በሱዳን ቆይታቸው የኤርትራን እና የሱዳንን የሁለትዮሽ ትብብሮችን ማጠናከር በሚቻልባቸው ላይ የሚመክሩ ሲሆን፣ በቀጠናዊ ትብብር እና ውሕደት ዙሪያ ውይይቶችን እንደሚያደርጉም የኤርትራ ማስታወቂያ ሚኒስቴር የማነ ገብረመስቀል በትዊተር ገጻቸው አስፍረዋል። (ኢዛ)

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ