የረቡዕ ግጥም ፪ኛ ዓመት፣ ፳
ዛሬ ጊዜ ሰጥቶህ እኔን ብታጠፋ
አታመልጥም አንተም ከመሞት ወረፋ
ያተረፍከው ሲታይ ኋላ ተጠቃሎ
መብለጥህ ብቻ ነው በክፋትህ ኪሎ
ሙሉውን አስነብበኝ ...ዛሬ ጊዜ ሰጥቶህ እኔን ብታጠፋ
አታመልጥም አንተም ከመሞት ወረፋ
ያተረፍከው ሲታይ ኋላ ተጠቃሎ
መብለጥህ ብቻ ነው በክፋትህ ኪሎ
ሙሉውን አስነብበኝ ...መተካት ቢችልም ሰውን ሰው አፍርቶ
ዓለም ተለውጧል የድሮ ሰው ጠፍቶ
መሠልጠን ነው ካልነው አዎ ሠልጥነናል
ያንኑ ያህል ግን ሰውነት አጥተናል
ሙሉውን አስነብበኝ ...ጉድ ብለን ነበረ በጃንሆይ እስር
ታላቅ መንግሥታቸው በደርግ ሲደፈር
ደርግም ተወራጭቶ ብን ብሎ ጠፋ
የዚህኛው ታየኝ ከሁሉም ሲከፋ
ሙሉውን አስነብበኝ ...ፕ/ር ፍቅሬ ቶሎሳ
ፊት ለፊትህ ሰው ጠኔ ይዞት
በቁንጣን እያገሳህ ልብህ ቢደነድን፣
ለተራበው አዝነህ ባትመግበው
አንተ የኖርክ ቢመስልህም ነህ በድን።
ሙሉውን አስነብበኝ ...ወለላዬ ከስዊድን
በሥራው ላይ ልፈላሰፍ
ቅኔ ልቀኝ ግጥም ልጽፍ
ቸኩያለሁ አልሞት ብሎኝ
የማደንቀው ሰው ነበረኝ
ሳይሞትማ ሳይቀበር
ስሙን ማንሳት እሱን ማክበር
መስሎ ታይቶኝ ልምድን መስበር
የማደንቀው ሰው እያለኝ
ልጽፍለት ተቸገርኩኝ
ሙሉውን አስነብበኝ ...