ሰቆቃወ ወገን (አበራ ለማ)
አበራ ለማ
ረሀብ፣ ስቃይ እንግልቱ - መች አንሶህ አንት ወገኔ
ስደትን ምርኩዝ አድርገህ - መግባትህ ከምድር ኩነኔ?
ምን ሊበጅህ? ምን ሊቤዥህ? ከቤት እሳት ከደጅ እሳት
ማምለጫ የለህ መሸሸጊያ - መድረሻ የለህ አንዳች ጥጋት፤
ክብር ኩራትህ - እንደራፊ ተላይህ ላይ ተቀዶ
ኢትዮጵያዊ ስምና ሰንደቅ - ማላገጫ ሲሆን እባር ማዶ፤
ማን ያስጥልህ? ማን ይድረስልህ ወገኔ?
ማን ይዋስህ? ማን ይሁንህ ምስለኔ?
ባለቤቱ ያቀለለውን አሞሌ
መች ባለ'ዳ ሊል ቢሮሌ? ...



