ስብሐት ለጨለማ (መስፍን ወ/ማርያም)

ስብሐት ለጨለማ

መስፍን ወልደማርያም (እንጉርጉሮ) - 1967 ( Read on PDF )

ስብሐት ለጨለማ፤ ለብርሃን ዋዜማ!

ጨለማ! የስርቆሽ ውድማ! የግብዝ ከተማ!

ጨለማ! የክፋት፤ የተንኮል፤ የጭካኔ አለኝታ!

የወንጀል ነፃነት! የኃጢአት ደስታ!

ይጠየቅ ሰው ሁሉ፤ እውነቱን ይናገር፤ የሚናገር ቢኖር፤

ብርሃን ነው ጨለማ ሰውን የሚያሳፍር?

ጨለማን ይጠላል ሰው ጨዋ ለመባል፤

ብርሃን ሲያሸማቅቅ አያውቀው ይመስል!

ሙሉውን አስነብበኝ ...