አስጠለለው (ክንፈሚካኤል ገረሱ)
ክንፈሚካኤል ገረሱ
ላ'መታት ያፈራ አንድ የቡና ተክል፣
ድንገት ተመልክቶ ብሳና ሲበቅል።
ከስሩ አቀርቅሮ ሲውተረተር ሲጥር፣
ጨረር ሙቀት ሽቶ አሻቅቦ ሲያማትር።
ቢያንኳስስ ቢያቀለው ጠኖ በግዝፈቱ፣
አቆልቁሎ ቢያየው ተንዛፎ ካናቱ።
ሙሉውን አስነብበኝ ...
ክንፈሚካኤል ገረሱ
ላ'መታት ያፈራ አንድ የቡና ተክል፣
ድንገት ተመልክቶ ብሳና ሲበቅል።
ከስሩ አቀርቅሮ ሲውተረተር ሲጥር፣
ጨረር ሙቀት ሽቶ አሻቅቦ ሲያማትር።
ቢያንኳስስ ቢያቀለው ጠኖ በግዝፈቱ፣
አቆልቁሎ ቢያየው ተንዛፎ ካናቱ።
ሙሉውን አስነብበኝ ...
የሌላ ሰው ስንጥር
ሲመታው ያደገ የግፈኛ ጥፊ
መስማማት አይችልም ሆኖ ሆደሰፊ
የሱ ሳይታየው የጨበጠው በትር
ትረብሸዋለች የሌላ ሰው ስንጥር
ሙሉውን አስነብበኝ ...
አንዳንዴ ተቆጣ
ከሆነ ሥራዬ የሱን ሐሳብ ማጽደቅ
አልሰበሰብም እንኳን ለጸብ፤ ለእርቅ
በልና ተናግር እንቢ ብለህ ውጣ
በእሽታ አትኑር አንዳንዴም ተቆጣ
ሙሉውን አስነብበኝ ...
ክንፉ አሰፋ
በታሪከኛዋ አምስተርዳም ከተማ በሚገኝ አንድ የሲኒማ ማዕከል ውስጥ የአበሻ ዘር ታጭቋል። ቲያትር ቤቱ ጢም ያለው ቲያትሩ ከመጀመሩ ከሰዓታት በፊት ነው። ወትሮውን በዚህ ሁኔታ ኢትዮጵያዊ በግዙፍ አዳራሽ ውስጥ ሞልቶ የሚታየው በጸሎት ቤቶች ብቻ ይመስለኛል። ምሽት ላይ የሚደረጉ የአበሻ ኮንሰርቶችም ቢሆኑ አረፋፍደው ነው የሚሟሟቁት። በዚህኛው እንግዳ ክስተት አግራሞቴን ገና ሳልጨረስ፣ ሌላ ነገር አየሁ። ትያትሩን ጨርሼ ስወጣ በሩ ላይ ሕዝብ ለሁለተኛው ዙር ተሰልፏል። … ከሰዓት እረፍት በኋላ “የቴዎድሮስ ራእይ”ን በአምስተርዳም ደገሙት!
ሙሉውን አስነብበኝ ...አብርሃም በየነ
የታጨደው ሳር ድርቆሽ ነው የከብቶች መኖ በመሆን
በበሬ ጫንቃ ድካም ጠግቦ አደር ያደረገን፤
የሞተው የግጦሽ ሳር ነው ጮሌ ፈረስ አሳድጎ
በጦር ሜዳ የድል ብሥራት ያቀዳጀን ጀግና ተዋጊ አድርጎ፤
የበሬውን ቆዳ ከበሮ የበሬውን አንጀት ጅማት
የፈረሱን ሞት በደል የሸንበቆውን ያካል ስብራት፤
ሙሉውን አስነብበኝ ...