ለሱማሌ መፍትሔ የአራትዮሽ ውይይት መጀመር ያስፈልጋል
ዳኮታ የጥናት ማዕከል
(አልሽባብ፤ ኢትዮጵያዊ ኃይል፤ የኤርትራና የአሜሪካ መንግሥት)
ሱማሌ የአልሽባብ ተዋጊዎች 98%፤ እነመለስና አሜሪካኖች ሊያቆሙት የሚፈልጉት መንግሥት ሁለት በመቶውን የሱማሌ ግዛት ተቆጣጥሮ ነው ያለው። መንግሥት ተብዬው እራሱን ከአልሽባብ ታጋዮች ከመከላከል በስተቀር ለማጥቃትና ይዞታውን ለማስፋፋት ምንም አቅም የለውም። እስከጭራሹም ሱማሌን ለቆ እንዲወጣ ቀነ ቀጠሮ እየተቆረጠለት ነው ያለው። የበዙት የህዝብ ተወካዮች፤ የመንግሥቱ ባለሥልጣናት ወደተለያየ ሀገር ጥለው ፈርጥጠዋል።



