የአድዋ ድል "በዕድል”?
ከ"ዓለም አቀፍ የኢትዮጵያውያን ባለሙያዎች ዕውቀት መለዋወጫ መረብ" የተሰጠ አስተያየት

የትግሬ ነፍጠኛ፣ የሸዋ ፈረሰኛ፣ የጎጃም እግረኛ፣ የአማራ ስልተኛ ከቦ ይቀላው፣ ያናፋው፣ ያንደገድገው ጀመር። ከእንዝርት የቀለለ የጁየ፣ ከነብር የፈጠነ ቤጌምድር፣ ከቋንጣ የደረቀ ትግሬ፣ ከአሞራ የረበበ ሸዌ፣ ከንብ የባሰ ጎጃሜ እያባረረ በየጎዳናው ዘለሰው። አውሬ የነጨው ነጭ መንጋ እየመሰለ በየዱር ሆዱን ገልብጦ ወደቀና የአሞራ ቀለብ ሆነ።[1]
መጋቢት ፲፭ ቀን ፪ ሺህ ፱ ዓ. ም.
በወለላዬና በዶክተር ተድላ ሃሳብ ላይ ተጨማሪ፣
በቅድሚያ ክብር በደምና በአጥንታቸው አንድነት አገር ላቆዩልን ለአድዋ ጀግኖች በሙሉ፣ ወለላዬ በስዊድን የመቶ ሃያ አንደኛው ዓመት የአድዋን ድል መዘክርና በዝግጅቱ ላይ የነበሩትን ክስተቶች ስላሳወቁን ብቻ ሳይሆን ምላሽ በመስጠትዎና ለሚመለከተውም ጥሪ በማድረግዎ ምስጋናችን የላቀ ነው። በእኛም በኩል የመቶ ሃያ አንደኛው ዓመት የአድዋን ድል በመጣጥፎች ለመዘከር ዝግጅት በምናደረግበት ጊዜ አንዳንዶቻችን የእቴጌ ጣይቱን ታላቅ አስተዋጽዖ ለብቻው ማዘጋጀት ጀምረን፣ ነጥለን የምናወጣው ታሪክ ጎደሎ ሆኖ ስላገኘነው አድዋን ከመላው ጀግኖቹ ጋር መተረኩ የተሟላ ሆኖ አግኝተነዋል። (የወለላዬን ጽሁፍ ለማንበብ እዚህ ይጫኑ!) | (የተድላ ደ. ተክሌን (ዶ/ር) ጽሁፍ ለማንበብ እዚህ ይጫኑ!)
ሙሉውን አስነብበኝ ...








