አዳማ ከኦሮሚያ የመውጣት መብቷ ሊከበር ይገባል
ይመር አብዶ

የአዳማ ልጅ ነኝ። እዚያው ተወልጄ ያደኩ። አባቴ ኦሮሞ ሲሆን እናቴ ጉራጌ ናት። አባቴ ኦሮምኛ ይናገራል። ግን ቤታችን የሚነገረው አማርኛ ነው። በአብዛኛው የናዝሬት ነዋሪ አማርኛ ተናጋሪ ነው። በከተማዋ በየመንገዱ በብዛት የሚነገረው አማርኛ ነው። አዳማ ናዝሬት እንደ አዲስ አበባ ናት ማለት ይቻላል።
ሙሉውን አስነብበኝ ...የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5





ይመር አብዶ

የአዳማ ልጅ ነኝ። እዚያው ተወልጄ ያደኩ። አባቴ ኦሮሞ ሲሆን እናቴ ጉራጌ ናት። አባቴ ኦሮምኛ ይናገራል። ግን ቤታችን የሚነገረው አማርኛ ነው። በአብዛኛው የናዝሬት ነዋሪ አማርኛ ተናጋሪ ነው። በከተማዋ በየመንገዱ በብዛት የሚነገረው አማርኛ ነው። አዳማ ናዝሬት እንደ አዲስ አበባ ናት ማለት ይቻላል።
ሙሉውን አስነብበኝ ...የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5





ግርማ ካሳ

መርጋ ኢብሳ የተባሉ ጦማሪ የአዲስ አበባና አካባቢዋን ሕዝብ በተመለከተ የሚከተለውን አስተያየት ሰጥተው አነበብኩኝ። ትንሽ አሳቁኝም አናደዱኝም።
"ኦሮሚያ/ሸዋ ውስጥ ያሉ በትምክተኝነት ምክንያት ኦሮምኛ ያልቻሉ ጥቂት ማኅበረሰቦች ካሉ ሁለት እድል አላቸው። አንደኛ ኦሮምኛን ለምደው ተስማምተው የክልሉን ሕግ አክብረው መኖር። ሁለተኛ ትምክተኝነት የሚወጥራቸው ከሆነ ደግሞ ወደመጡበት በፍላጎት ሄደው በክልላቸው እንደፈለጋቸው መሆን ይችላሉ። ከዚህ ውጭ ኦሮሞን በጎጥ ለመከፋፈል የምትጥሩትን የሚሰማቹ የለም። ኦሮሞ አንድ ነው። ሁሉም የቦረኔ ባረንቱ ልጅ ነው። ሸዋ ሲነካ ወለጋ ተነካ፤ ሐረር ሲነካ ጅማ አርሲ፣ ባሌ፣ ሸዋ፣ ጉጂ፣ ቦረና፣ ኢሉ፣ ወሎ(ኦሮሞ)ን ያገባዋል። ኦሮሚያ ስትኖር ኢትዮጵያ ልትኖር ትችላለች። ኦሮሚያ ስትፈርስ ግን ኢትዮጵያ የምትባል አገር ቅዠት ትሆናለች“ ነው ያሉት እኝህ ጦማሪ።
ሙሉውን አስነብበኝ ...የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5





ባህር ከማል
እራስን ከጥቃት በመከላከል ሰላማዊ ህይወት ለመምራት ከሌሎች ሰዎች ጋር ተቻችሎና ተስማምቶ አብሮ የመሆን ባህርይ የሰው ልጅ በተፈጥሮ የሚያገኘውና በህወት ልምድም የሚያዳብር ችሎታ ነው ማለት ይቻላል። ይህ አብሮ የመሆን ልምድ ከቤተሰብ ጀምሮ በጉርብትና፤ በጎሳና ሀይማኖት መመሳሰል እያደገ አገርን እስከ መመሥረት ይደርሳል። በሂደትም አንድነት ኃይል መሆኑንም ያረጋግጣል። እነዚህ በየደረጃው ያሉት ስብስቦች በውስጣቸው ልዩነት መኖሩ አይካድም። ልዩነት በሀገር ደረጃ በተሰባሰቡ ሰዎች መሀከል ብቻ ሳይሆን በመንትዮች መሃከልም ይታያል። ሕዝቦች ልዩነታቸው አንደተጠበቀ ሆኖ በጋራ በሚያስተሳስራቸው፤ በሚያቀራርባቸውና ባሳለፏቸው ታሪካዊ አብሮነት ተመስርተው አንድነትን ፈጥረው በድንበር የተከለሉ አገራትን መስረተው አብረው ይኖራሉ።
ሙሉውን አስነብበኝ ...የአንባብያን ድምፅ: 4 / 5





ተሻለ መንግሥቱ

እንዳጀማመራቸው አምሮባቸው የሚያልቁ ነገሮች ቢኖሩ በጣም ጥቂት መሆን አለባቸው ብዬ አምናለሁ። እንጂ ድል ባለ ድግስ የተዳሩ ጥንዶች በፍቺ ወይ በሞት እንደሚለያዩ፣ ብን ባለ ፍቅርና ወዳጅነት ውስጥ የነበሩ ግለሰቦች ወይም ቡድኖች አንዳች ነገር በመሃላቸው ገብቶ እንደሚመነቃቀሩና “ዐይንህ/ሽ ላፈር” እንደሚባባሉ … ፀሐይ የሞቀው ማኅበረሰብዓዊ እውነታ ነው። እናም እውነትም እንዳማረ አይገድልም - ማለቂያም ሁሉ እንደጅማሮ አያምርም።
ሙሉውን አስነብበኝ ...የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5





ነፃነት ዘለቀ

ይሄ የቁጥር ነገር አልገባኝ እያለ መቸገሬን የምገልጥላችሁ አገሬ ውስጥ በምታዘበው የሙስና ግዝፈት እያፈርኩና እያረርኩም ነው። ትንሹም ትልቁም ከመሬት እየተነሣ “አንድ መቶ ሚሊዮን ከባንክ ተበድሬ ...፣ አምስት መቶ ሚሊዮን ብር ከባንክ ተበድረን ስናበቃ ...፣ ለእገሊት 30 ሚሊዮን አበድሬያት ...” እያለ ሲያወራ አንደበቱን ያዝ እንኳን አያደርገውም።
ሙሉውን አስነብበኝ ...የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5





ይገረም አለሙ

መንደርደሪያ፤ ብዙ ግዜ አዲስ ያልሆኑ ግን እኛ አዲስ የተፈጠሩ ያህል የምንጮህባቸው ነገሮች ሲከሰቱ ብዙዎች የሚያሳዩት ነገር “የጅብ ችኩል ቀንድ ይነክሳል” ይሉ አይነት ነው። ወያኔ ሥልጣኔን ያሰነብትልኛል ብሎ እስካመነ የማይቆፍረው ጉድጓድ እንደሌለ እየታወቀ ድርድር ጠራ ተብሎ፤ ተቀዋሚ ተብየዎችም ጥሪውን ተቀብሉ ተብሎ፤ አዲስ ተአምር የተፈጠረ ይመስል ድጋፍና ተቃውሞ በተለመደው መንገድ እየተሰማ ነው። ነገር ግን ከተለመደውና መረጃም ማስረጃም ፍለጋ ከማያደክመው የፍረጃና ውንጀላ ጉዞ ወጣ ብሎ ድርድር ለምን፣ ድርድር በእነማን መካከል፣ ድርድር እንዴትና በምን ሁኔታ? ወዘተ የሚሉት ጥያቄዎች መመለስ የሚችል አስተያየት መጻፉ፣ ልምድ ማካፈሉ ነበር የሚበጀው። እኔ ይህን ለማድረግ የሚበቃ እውቀትም ልምድም የለኝም። ፍረጃና ውንጀላ ላይ በመሮጥም ሆነ ጭፍን ድጋፍ በመስጠት ደግሞ አላምንም፣ በዚህ መካከል ሆኜ ስለ ድርድሩ የተሰማኝን ልበል።
ሙሉውን አስነብበኝ ...