ርጥቡ ሬሳ ደረቅ ያስነሳ
ይገረም አለሙ

ዛሬ ጥቅምት አንድ ቀን 2009 ዓ.ም. ቀትር ላይ በሞት የተለዩንን ኢ/ር ኃይሉ ሻውልን ወደ ዘለዓለማዊው ቤት ለመሸኘት አዲስ አበባ አራት ኪሎ ከሚገኘው ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ቤተ ክርስቲያን ተገኝተናል። እዛው የተገናኘን ሰዎች ዝናቡ መቆሚያ ቢያሳጥንም አንድ ጥግ ይዘን አስክሬናቸው እስኪደርስ ወግ ይዘናል። ኢ/ር ኃይሉን ለመጀመሪያ ግዜ ያወቅናቸው በመአህድ ከዚያም በመኢአድ ቀጥሎም በቅንጅት፤ እንደገና ተመልሶ በመኢአድ በመሆኑ ከዚህ እውቀታችን በመነሳት ከፊት ወደ ኋላ እያስታወስን ስናነሳ ስንጥል የመአህድ መስራችና ፕሬዝዳንት የነበሩትንና በእስር ተሰቃይተው በግፍ የሞቱትን ፕ/ር አስራት ወልደየስን አስታወስን። የገደሉንንም የሞቱልንንም እኩል የምንረሳ ምን ጉዶችን በማለትም ራሳችንን ወቀስን።
ሙሉውን አስነብበኝ ...








