ለጥምቀት ያልሆነ ቀሚስ ለመቼ ሊሆን ነው?

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

ግርማ በላይ

Amhara protesters

“ዝምታ ወርቅ ነው” - ጥሩ አባባል ነው። “ዝም አይነቅዝም” - ይሄኛውም ግሩም አባባል ይመስላል። “በለፈለፉ በአፍ ይጠፉ” - ጠንከር ያለ ሀበሻዊ መልእክት ያለው ነው፤ ፀረ ዴምከራሲያዊነቱም እንዲሁ ከሌሎቹ አየል ይላል። አዎ፣ የሀገራችን ሥነ ቃላችንም ሆነ አጠቃላይ ባህላዊ ትውፊታችን መናገርንና ሃሳብን በነፃነት መግለጽን አያበረታታም ብቻ ሣይሆን ክፉኛ ይኮንናል። በዚህም ሳቢያ ይሉኝታ እየገነነና ሀፍረትን እየወለደ “የዝምታ የዝምታ” የሚል አንደርብ የተደገመብን ይመስል፤ ውስጥ ለውስጥና በየመሸታ ቤቱ እየተማማን እንኖራለን።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አለባብሰው ቢያርሱ ባረም ይመለሱ

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

ይሄይስ አእምሮ

Bishoftu protest 2nd Oct, 2016. (Photo AP)

ማለባበስ በጣም ጎጂ ነው። አሁን የምንገኝበት ማኅበራዊና ፖለቲካዊ አጣብቂኝ እንደእስከዛሬው ዓይነት የሽፍንፍንና የጥግንግን አካሄድን የሚያስተናግድ አይደለም - አምርሯል። አካፋን አካፋ ማለት የሚገባበት ትክክለኛ ጊዜ ላይ ደርሰናል። አንድን እውነት ሺህ ጊዜ ብንሸፋፍነው መገለጡ አይቀርም። ሲገለጥ ደግሞ የሚያስቀይም ስዕል ጎልቶ የሚታይበት አጋጣሚ እየበዛ ይመጣና ከመገናኘት ይልቅ መለያየት የማያመልጡት አሳዛኝ ክስተት ይሆናል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የቢሾፍቱው እልቂት

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

ይገረም አለሙ

Irrecha protest, 2nd Oct, 2016

ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲተላለፍ የኖረውን የኢሬቻ በዓል ለማክበር ኢትጵያውያን በቢሾፍቱ/አዳማ ከተማ የከተቱት ቅዳሜ መስከረም 21 ቀን 2009 ዓ.ም. ጀምሮ ሲሆን፣ በማግስቱ እሁድ ረፋዱ ላይ በምስል ተደግፎ በማኅበራዊ መገናኛ የተሰራጨው ዜና ፈጽሞ ያልተጠበቀ ብቻ ሳይሆን፤ ሊገመት የማይችል ነበር። በአንድ ጣራ ስር ሆነን መርዶውን ከሰማነው መካከል ዕድሜአቸው ስድሳውን የዘለለ አንዲት እናት ለስንቱ እናልቅስ ብለው አንባቸውን አዘነቡት። ሌሎቻችንም በየውስጣችን አለቀስን። ለደቂቃዎች ቤቱ ጸጥ ረጭ አለ። ሁሉም በየራሱ ስሜት ውስጥ ሰምጦ የሚናገር ጠፋ። ዝምታው የተሰበረው ሆራ ኃይቅ ዳር የተሰበሰበ ህዝብ አይደለም ሰላማዊ ተቃውሞ ማሰማት ድንጋይ ቢወረውር ምን ጉዳት እንዳያደርስ ነው በአስለቃሽ ጭስ የሚባረረው በጥይት የሚደበደበው በሚል መልስ የለሽ ጥያቄ ነበር።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ህወሓት የማይወድቅባቸው የትግል ሥልቶች

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

ነፃነት ዘለቀ

Irrecha protest 2nd Oct, 2016.

ባሳለፍነው እሁድ በደብረ ዘይት የኢሬቻ በዓል አከባበር ላይ በአጋዚ የወያኔ ቅልብ ጦር ሕይወታቸውን ያጡ ወገኖቻችንን ነፍስ እግዚአብሔር ይማርልን! ከዚህች ዘግናኝ ቀን በፊትም ሆነ በኋላ በተለያዩ የሀገራችን አካባቢዎች በዚሁ የወያኔ ጦር ያለቁና ወደፊትም የሚያልቁ ወንድም እህቶቻችንንና ልጆቻችንን መንግሥተ ሰማይን ያውርስልን። ፈጣሪ የነሱን መስዋዕትነት እንደአቤል ንጹሕ ደም ቆጥሮልን የነፃነታችንን ቀን ያፋጥንልን። የቤተሰባቸውንም ሆነ የሁላችንን የተሰበረ ልብ ይጠግን። አሁንስ እጅግ በጣም እየተጎዳን ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ለዘብተኞችን ማጥቃት፤ አክራሪዎችን ማብዛት

የአንባብያን ድምፅ: 4 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Inactive

አንዱዓለም ተፈራ

Irrecha protest, 2nd Oct 2016

የሃሳብ ልዩነት፤ ያለ ነገር ብቻ ሳይሆን፤ አስፈላጊም ነው። የተለያዩ ሃሳቦች መከሰት፤ አማራጮችን በመድረክ ላይ በማቅረብ፤ ልዩነቶችን እንድንመረምርና፤ በብዙኀኑ ዓይን የተሻለ የተባለውን እንድንመርጥ ዕድል ይፈጥርልናል። ከነዚህ የተለያዩ ሃሳቦች ተነስቶ ርስ በርስ መወነጃጀሉ፤ አንድም እኔ ያልኩት ብቻ ይሁን ባይነት ብሎም ራስን የማግዘፍ ጥንውት ነው። ሌላም ትግሉ መልክ ይዞ ወደፊት እንዳይሄድ እንቅፋት ለመሆን የተጠነሰሰ ሴራ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የታሪክ ሂደት ርቃናችንን እንዳያስቀረን

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

ይገረም አለሙ

የመብትና የነጻነት ጥያቄ በኢትዮጵያ

ገና እንደባተ ታዋቂ ኢትዮጵያውያንን በተከታታይ ነጥቆ ኀዘን ያስቀመጠን የተሰናበተው የግፍ ዓመት ሊባል የሚችለው 2008 ዓ.ም.፤ የሞት መርዶ፣ የእስር፣ እንግልትና ስቃይ ዜና ሳይለየው ከል እንዳለበሰን ነው ወደ 2009 ዓ.ም. የተሸጋገርነው። ፈጣሪ በቃችሁ ካላለን በስተቀር፤ የ2009 ዓ.ም. አጀማመርም አስፈሪ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ