አገራዊ የጸሎትና ምህላ ጥሪ
ምሕረት ዘገዬ
የአገራችን ጉዳይ ከድጥ ወደ ማጥም አልፎ ልንገልጸው ቃል ያጣንለት የመቅሰፍቶች ሁሉ ትንግርታዊ ትዕይንት ሆኖኣል። አንዱ ቀን አልፎ ሌላው ሲተካ ከመሻሻል ይልቅ እየባሰበት ሄዶ ዜጎች በቋሚነት ወላፈኑ በማይበርድ ምድጃ ላይ ተጥደው እንዲቃጠሉ ተፈርዶባቸዋል። በዚህም ምክንያት የምናደርገው ጠፍቶን ብዙዎቻችን በአገራችን የወደፊት ዕጣ ፋንታ ላይ ክፉኛ ተጨንቀን ተጠበናል። የዚህች ታሪካዊ አገር መጥፋት የሚያስደስታቸው ካልሆነ በስተቀር ጤናማ ለሆነ የዓለም ዜጋ ለኛ ለኢትዮጵያውያን የተደገሰልን መከራ እጅግ ዘግናኝ ነው። በዚህን ወቅት አገር አማን ብሎ የሚተኛ፤ ከዚያም ባለፈ በእህል ውኃ ስካርና ጥጋብ ጮቤ የሚረግጥ ካለ ዓለም ብታልፍ የማያሳስበው ግዴለሽ እንጂ የሚያስብ አንጎል ባለቤት የሆነ ጤናማ ሰው አይደለም።
ሙሉውን አስነብበኝ ...





