ፀረ-ማርያም ፖለቲካ

Star InactiveStar InactiveStar InactiveStar InactiveStar Inactive

ማርያም Mariamተስፋዬ ገብረአብ

ስብሃት ነጋ፣ በፓልቶክ ክፍል ተጋብዞ ባደረገው ንግግር፣ “ለኦርቶዶክስ ወይም ለአማራ ብቻ ተወስኖ የቆውን የኢትዮጵያ መንገስታዊ ስልጣን ለተጨቆነው ህዝብ አስረከብነው” ማለቱን አንድ ጓደኛዬ ነገረኝ። ይህን የነገረኝ ጓደኛዬ በስብሃት ንግግር በጣም ተገርሞ ስለነበር፣ “አታስብ! ስብሃት አብሻቂ የንግግር ጠባይ አለው።” ስል ጠቆምኩት። ለነገሩ በሚናገረው ባልስማማም፣ ስብሃት ያመነበትን እንደወረደ ስለሚያፈርጠው ከሌሎቹ እሱ ይሻለኛል። “በዚህች አለም ላይ መጥፎም ይሁን ጥሩ ያመንክበትን ፈፅመህና የልብህን ተናግረህ ማረፍን የመሰለ እርካታ የለም” ይል ነበር መለስ ዜናዊ - ነፍሱን ይማረውና።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ጉዱ ካሳ እና “ሰበነክ-ሊቃውንት”

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

ኤፍሬም እሸቴ

እንግሊዛዊ ሆኖ “ሼኪስፒርን የማያውቅ፣ ሥራዎቹንም ያላነበበ፣ ኢትዮጵያዊ ሆኖ ሀዲስ ዓለማየሁን የማያውቅ ‘ፍቅር እስከ መቃብርን’ም ያላነበበ” ቢኖር እጅግ የሚደንቅ ይሆናል። እንዲያውም ጥያቄው ‘ስንት ጊዜ አነበብከው?’ እንጂ ‘አንብበኸዋል እንዴ?’ አይሆንም የሚል ግምት ነበረኝ። ከዕለታት በአንዱ ቀን በድሮ የትምህርት ቤት መጽሐፎቻችን ውስጥ ስላሉ ታሪካዊ ጽሑፎች ስናወጋ በመካከሉ አብዲሳ አጋን አስታወስን። “ስንተኛ ክፍል መጽሐፍ ውስጥ ነበር ጃል?” እያልን ስንጠያየቅ አጠገባችን የነበረ አዕምሮው ብሩህ የሆነ ልጅ እግር የዩኒቨርሲቲ መምህር “ማነው አብዲሳ አጋ?” የሚል ጥያቄ አቀረበ። በመጀመሪያ እንደ ቀልድም ወሰድነው። ቀጥሎ እንደ መገረምም አደረገን።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የሃይለማርያም አንገት

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

ሃይለማርያም ደሳለኝ Hailemariam Desalegneተስፋዬ ገብረአብ

ዶክተር ነጋሶ ጊዳዳ ፕሬዚዳንት ሆነው በተመረጡ ጊዜ በመከላከያና በሲቪል የህወሃት አባላት ዘንድ አቧራው ጨሶ እንደነበር አስታውሳለሁ። አባላቱ የፖለቲካውን ጨዋታ አልተረዱትም ነበር። በወቅቱ የነጋሶ ሹመት የይስሙላ መሆኑን ማስረዳት፣ ለህወሃት መሪዎች ፈተና ሆኖባቸው ነበር። ህወሃት አሁንም ተመሳሳይ ችግር ገጥሞታል። ምናልባትም በቀጣዩ የሃይል አሰላለፍ የህወሃት የበላይነት እንደተጠበቀ መሆኑን ማሳመን ካልቻሉ መፈንቅለ መንግስት ሊያጋጥም ይችላል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ተሸናፊው ሶፊያን አህመድ ነበር

Star InactiveStar InactiveStar InactiveStar InactiveStar Inactive

አቶ በረከት ስምዖን Ato Bekreket Semeonተስፋዬ ገብረአብ

የኢህአዴግ ምክርቤት ጉባኤ ተጠናቆአል። ምክር ቤቱ ሃይለማርያምና ደመቀን ዋና እና ምክትል አድርጎ መርጦአል። በዚህ ምርጫ አነጋጋሪ የሆነው፣ ከምርጫው በፊት፣ “ታጋይ የነበረ ለምርጫ አይቀርብም” በሚል ማሳሰቢያ ከበረሃ የገቡ ታጋዮች ሁሉ ራሳቸውን ከምርጫ ማግለላቸው አንዱ ነበር። በጥቆማው ወቅት ከህወሃት እጩ ሆኖ ለውድድር የቀረበ አለመኖሩ ሌላው አነጋጋሪ ጉዳይ ሆኖአል። ሶስት ሰዎች ተጠቆሙና ሁለቱ ተመረጡ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በጎ ምክር ለጓዶች

Star InactiveStar InactiveStar InactiveStar InactiveStar Inactive

ተስፋዬ ገብረአብ

የኢህአዴግ የስልጣን ሽኩቻ ተባብሶ በመቀጠሉ የአመራር አባላቱ ዝግ ስብሰባ ላይ ስለመሆናቸው እየተሰማ ነው። ይህን ሽኩቻ ከህዝብ ጆሮ ለመሰወር ሲባል ስለ ኢህአዴግ ስራ አስፈፃሚ ስብሰባ በቴሌቪዥን የተላለፈው ቀሽም ድራማ ነበር። የአመራር አባላቱ እጃቸውን እያወጡ ድምፅ ሲሰጡ በቲቪ ይታያል። በምን ጉዳይ ላይ ነው ተከራክረው በድምፅ ወሰኑት? አልተገለፀም። ከኢህአዴግ ነባር ልምድ አንፃር፣ ከስብሰባው በፊት ጋዜጠኞች ገብተው ምስል ቀርፀው እንዲወጡ እንደሚደረግ አውቃለሁ። ከዚያም በሮችና መስኮቶች ተዘግተው ስብሰባው ይቀጥላል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የአገር መሪ ሲሞት (ኤፍሬም እሸቴ)

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

ኤፍሬም እሸቴ (www.adebabay.com)

በሕይወቴ ኢትዮጵያ መሪ ሲሞትባት አላየኹም። ቀዳማዊ አጼ ኃ/ሥላሴ ሲወርዱ የሕልም ያህል ትዝ ይለኛል። ሞታቸውም እንደ ሕልም አለፈ። ከዚያ በኋላ የወታደራዊው መንግሥት ዘመን ብዙ ባለሥልጣናት ሲሞቱ መሪው ግን ምንም ሳይነኩ ቆዩ። ከዚያም የእርስበርስ ጦርነቱ መንግሥታቸውን ጠራርጎ ሲገነድሰው እሳቸው ወደ ዚምባብዌ ገቡ። አልሞቱም ዛሬም ድረስ። ከዚያ በኋላ ኢትዮጵያን የመሩት አቶ መለስ ዜናዊ፣ ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ እና ፕሬዚደንት ግርማ ወ/ጊዮርጊስ ናቸው። ከእነርሱ መካከል በሞት በመለየት አቶ መለስ ቀደሙ ማለት ነው። ነፍሳቸውን ይማር።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ