ሆነና ነገሩ የተገላቢጦሽ፣ አህያ ወደ ቤት ውሻ ወደ ግጦሽ
ይገረም አለሙ
አበው መሆን ያለበት ቀርቶ የማይሆነው ሲሆን፣ ያለ አባቱ ያለወግ ሥርዓቱ የሆነ ነገር ሲያጋጥማቸው የሚገልጹበት ይህ አባባል ተቀዋሚ ተብሎ ለተሰለፈው ግን ምን ለምን እንዴት? አንደሚወም ለማያውቀው ቢያወቅም በወሬ እንጂ በተግባ ለማይገኘው ወገን ድርጊት በጣሙን ገላጭ ይመስለኛል። ድርጊት እየጠቀሱና ማስረጃ እያጣቀሱ በዚህ አባባል የሚገለጹ በርካት ጉዳዮችን ማንሳት የሚቻል ቢሆንም ለዛሬ ግን አንዱን ብቻ በእጅጉ የተጠናወተንን የመርሳት በሽታ/ችግር ብቻ ላንሳ። ግን ከዛ በፊት ርእስ ያደረኩትን አባባል ባስታወሰኩ ቁጥር ፈጥኖ በአእምሮየ የሚመጣ አንድ ነገር አለ፣ ፕሮፌሰሩ ከአሜሪካ ወደ ትግል ሜዳ ኮረኔሉ ከትግል ሜዳ ወደ አውሮፓ ከአባባሉ ጋር የተዛመደ አይደለም ትላላችሁ። ኮረኔሉ ግዴለም መሄዱን ይሂድ እዛ ሆኖ ታጋይ ነኝ ማለቱ እንዲህም ብሎ አጃቢና ተከታይ ማግኘቱ ግን አዬ! እኛ ያሰኛል።
ሙሉውን አስነብበኝ ...









