የወያኔ የዝርፊያ ድርጊት - በኤርምያስ ለገሰ የመለስ ልቃቂት

ይገረም አለሙ

አዩትና ልቡ እንደሞተበት

አባቱ ቀየ ላይ ወርደው ጠመዱበት

የመለስ ልቃቂት መጽሐፍ
"የመለስ ልቃቂት" የኤርምያስ ለገሰ መጽሐፍ

የኤርምያስ ለገሰን የመለስ ልቃቂት መጽሐፍ እያነበብኩ ነው። የወያኔ የዝርፊያ ድርጅቶችን አይነትና ብዘት በተለያየ ግዜ በተለያየ መንገድ እየተነገረም እየተጻፈም ያውቃናቸው ቢሆንም ይህን ያህል ዝርፊያ መፈጸማቸውን የሚያውቅ ብዙ ሰው የነበረ አይመስለኝም። ኤርምያስ የካድሬነት ቆይታውም ሆነ የኮሙኒኬሽን ምኒስቴር ዲኤታነቱ ዘራፊዎቹን ድርጅቶች በቅርብ ለማወቅ ያስቻለው በመሆኑ የሚያስነብበን በመረጃ እና ማስረጃ የተረጋገጠ እውነት ልብ ያቆስላል። ከወያኔዎቹ ድፍረት የእኛ ዝም ብሎ ሀገር ማዘረፍ ጥያቄ ያጭራል ቁጭት ይፈጥራል። ግና እኛ ከሕወሓት በተቃራኒ የቆምን ነን የምንል ወገኖች ከአንድ ሳምንት የሚያልፍ ቁጭት፣ ንዴት፣ ምሬት፣ ወዘተ አያውቀንም እንጂ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ሞት ላይቀር፣ ተጠላልቶ መኖር

ይገረም አለሙ

የአቶ አሰፋን ነፍስ ይማር! በጥላቻ ለምንኖር የይቅርታ ልብ ይስጠን!

Assefa Chabo
አቶ አሰፋ ጫቦ

የት አባቱ ሞትም ይሙት!
እባካችሁ ዘመዶቼ ስሞት ሞትም አብሮኝ ይሙት
በሳቅ በደስታ ግደሉት
በሀሴት በእልልታ ውገሩት
ከአጥንት በታች ቅበሩት
እባካችሁ ለሞት የልብ ልብ አትስጡት
ናቁት አጥላሉት አውግዙት
በሙሾ ግነን አትበሉት
በሞቴ አታስደስቱት፣
(ሎሬት ጸጋዬ ገብረመድህን)

የሰው መጨረሻው ሞት እንደመሆኑ ሞት በራሱ አያሳዝንም፣ አሟሟቱ እንጂ፤ ያለ ግዜው መቀጨት፣ በአሳቃቂ ሁኔታ መሞት፣ እውቀቱን፣ ልምዱን ችሎታውን ለአገር ጥቅም ሳያውል ወይንም ጀምሮ ሳይጨርስ መሞት ወዘተ ያሳዝናል። ያስቆጫል። ሟች በሕይወት በነበረበት ግዜ ለቤተሰቡ ምሰሶ ከሆነ ቤተሰቡ ለአንድ ሰሞንም ቢሆን ያዝናል። ለአገር ለወገን ጠቃሚ የነበረ ከሆነ ሕዝብ ያዝናል። በእኛ ባህል ደግሞ ሰው ሲሞት ክፉው ደግ፣ ጨካኙ ሩህሩህ፣ ንፉጉ ቸር፣ ፈሪው ጀግና ተደርጎ ይነገርለታል የሕይወት ታሪክ ተብሎ ይነበብለታል። ምን መጥፎ ቢሆን ሙት አይወቀስም። ሙት ወቃሽ አታርገኝ ይላሉ አበው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ይህን ነበር የምፈራው

ብሥራት ደረሰ - ከአዲስ አበባ

ማስታወቂያ!
የመጀመሪያው የአማራ ዓለም አቀፍ ጉባኤ

ወያኔን እግዜር ይይለት! የኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች እንደሆኑ የሚታመኑ ምዕራባውያንም ይሁኑ ምሥራቃውያን እነሱም እግዜር ይይላቸው! በተለይ በተለይ የነዚህ የውጭ ምንደኛ ጠላቶቻችን አሽከር በመሆን ላለፉት 42 ዓመታት ኢትዮጵያን እንደደሮ ሲበልቱና ሕዝቧን እንደአሻሮ ሲቆሉ ሀብት ንብረቷንም በግላጭ ሲዘርፉና ወደጎሬኣቸው ሲያጓጉዙ የነበሩ ሰሜነኛ ናዚዎችና ፋሽስቶች ዘር አይውጣላቸው። የጀመሩት እንደጪስ በንነውና እንደጤዛ እረግፈው ወደታሪክ ትቢያነት የመለወጥ ትንቢታዊ የመጨረሻ ዕጣ በቅርብ ጊዜ ተጠናቆ ሀገራችን ነፃ እንድትወጣ ፈጣሪ ይርዳን። አሜን።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ፖለቲካም እንደ ሳይንስና እንደ ሂሳብ መታየት ያለበት ወይስ ሳይንስ-አልባ!

ፈቃዱ በቀለ (ዶ/ር)

መግቢያ

ፖለቲካን በሚመለከት ከሂሳብ አንፃር ሳይሆን ከሳይንስ አንፃር ብቻ ለመጻፍ ሳወርድ ሳወጣ፣ አቶ ካሳሁን ነገዎ የኤስ ቢኤስ ጋዜጠኛና ቃለ-መጠይቅ ጠያቂ እ.አ በ03.04.2017 ዓ.ም በፖለቲካና በሂሳብ መሀከል ስላለው ግንኙነት የሂሳብ አስተማሪና ተመራማሪ ለሆኑት ፕሮፌሰር ደጀኔ አለማየሁ ያቀረበላቸውን ጥያቄዎችና መልሶቹን ካዳመጥኩኝ በኋላ በዚህ አርዕስት ላይ ለመጻፍ ተገፋፋሁ። በመሰረቱ ለቀረቡት ጥያቄዎች የተሰጡትን መልሶች ካዳመጥኩኝ በኋላ በመልሱ በጣም መርካቴ ብቻ ሳይሆን፣ አገራችን ኢትዮጵያ እንደዚህ ዐይነት ምሁራንን ለማፍራት ችላለች ወይ? ብዬ ራሴን ትንሽ ለማጽናናት ሞከርኩኝ። በመሰረቱ ፕሮፌሰር ደጀኔ ፖለቲካ እንዴት ከሂሳብ ጋር ሊያያዝ ይችላል ተብለው ለተጠየቁት ጥያቄና ስለፖለቲካ ምንነት በደንብ ስላብራሩና አጥጋቢ መልስም ስለሰጡ ይህ ጽሁፌ የሳቸውን አተናተን የሚደግፍ ነው። ትንሽ የማክልበት ነገር ቢኖር ፖለቲካ የሚባለው ሕብረተሰብዓዊ ፕሮጀክት በአውሮፓ ምድር ውስጥ እንዴት አድርጎ ቀስ በቀስ ሊዳብር እንደቻለና ለዕድገትና ተቻችሎ ለመኖር የሚያስችል መሳሪያ በመሆን የተለያየ አመለካከት ባለቸው ፓርቲዎችና የሕብረተሰብ ክፍሎች ዘንድ ተቀባይነትን እንዳገኘ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ጠቅላይ ሚንስትራችንን በዚህች ትንሽ አጋጣሚ እንወቅ

ነፃነት ዘለቀ

PM Haliemariam Desalegn
ጠ/ሚ ኃይለማርያም ደሳለኝ

እንደአካሄድ ጠቅላይ ሚንስትሩን የማያውቅ ወይም ለማወቅ የማይጓጓ ዜጋ መኖር የለበትም። ምክንያቱም ጠቅላይ ሚንስትር ማለት ከእያንዳንዱ ዜጋ ልብ ውስጥ መጥፋት የሌለበት የሁሉም አለኝታና ከአባትና እናት የማይተናነስ ቦታ ያለው ነውና። አንድ ዕድለኛ ቤተሰብ ውስጥ እናትና አባት ይኖራሉ። አንዱ ቢጎድል ከሁለት አንዱ ይኖሩና ክፍተቱን በተቻለ መጠን ለመሙላት ይሞክራሉ። ሁለቱም ከጎደሉ ግን በተለይ ልጆች ትንንሽ ከሆኑ ብዙ ችግር ይፈጠራል። በተጨማሪም የወላጆች መኖር ብቻውን ምንም ማለት የማይሆንበት አጋጣሚ መኖሩንም መዘንጋት አይገባም።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

“አሥር ቢሊዮን” ብሩ በእርግጥ የወጣቱን የሥራ አጥነት ያቃልላል?

ዮፍታሔ

“ሪፖርተር” ከሰሞኑ ካወጣቸው ዘገባዎች አንዱ "ከወጣቶች አሥር ቢሊዮን ብር በጀት ተጠቃሚ ለመሆን ከሦስት ሚሊዮን በላይ ሥራ አጦች ተመዘገቡ" ይላል። ሲጀመር ሕወሓት ይህንን እቅድ ድንገተኛ ደራሽ በሆነ መንገድ በፓርላማ እንዲጸድቅ ያደረገችው የተፈጠረው ሕዝባዊ አመጽ አንዱ መነሻ ምክንያት የወጣቶች ሥራ አጥነት ስለሆነ ሥራ አጥነቱን በመቀነስ ሕዝባዊ አመጹን ማብረድ እችላለሁ ከሚል ስሌት ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የሕይወት ዋጋ

ፕ/ር መስፍን ወልደማርያም

በተደረመሰው ቆሻሻ ሕይወታቸውን ያጡ ወገኖቻችን የቀብር ሥነሥርዓት
በተደረመሰው ቆሻሻ ሕይወታቸውን ያጡ ወገኖቻችን የቀብር ሥነሥርዓት፣ ገብረክርስቶስ ቤተክርስቲያን፣ አዲስ አበባ፣ መጋቢት ፬ ቀን ፳፻፱። (ፎቶ፡ AP)

በ2009 ዓ.ም. ቆሼ የሚባል ሠፈር ወይም መንደር ተፈጠረ፤ ቆሼ ማለት ቆሻሻን ማቆላመጫ ነው፤ ቆሻሽዬ ማለት ነው፤ ቆሼ የቆሻሻ ተራራ ነው፤ በዚያ የቆሻሻ ተራራ ዙሪያ መሄጃ የሌላቸው ሰፈሩበት፤ ጥንት ሴትዮዋ እንዳለችው፡-

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ሦስቱ መስቀለኛ መንገዶች! ... ታሪክ እራሱን እንዳይደግም

መስቀሉ አየለ

ደርግ የሚባል ለኮንጎ ዘማቾች ደመወዝ ለማስጨመር ከየክፍለጦሩ የተወከለ የወታደሩ ኮሚቴ ግዜያዊ ጣቢያውን አዲስ አበባ በሚገኘው አራተኛው ክፍለ ጦር አቋቁሞ፤ ከኃይለሥላሴ መንግሥት ጋር መደራደር ጀመረ። ነገሩ በወቅቱ ከነበሩት ካቢኔቶች በላይ ሄደና እንደ ቀልድ ከንጉሡ በመድረሱ አጋጣማውን እየተጠቀመ ወደ ቤተመንግሥቱ ወጣ ገባ ለማለት ዕድል ያገኘው ይኽ ኮሜቲ የንጉሡን ክፉኛ መድከም ለማስተዋል ግዜ አልወሰደበትም።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ከኢሳያስ አፈወርቂ ቃለምልልስ በስተጀርባ

ክንፉ አሰፋ

ኢሳያስ አፈወርቂ
የኤርትራው ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ

ጠንቋይና ፖለቲከኛ የሚያመሳስላቸው አንድ ነገር አለ። ሁለቱም ተገልጋያቸውን ለማምታታት የትኩረት አቅጣጫ ማስቀየርን ተክነውበታል። ኢሳያስ አፈወርቂ በዚህኛው - የኦሮሚያ ሚዲያ ኔትወርክ - ገለጸቸው ራሳቸውን ሳይቀይሩ ሌላውን ለመቀየር የተነሱ ግብዝ ነው የሆኑት።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በሁዳዴ ጾም የአህያ ልኳንዳ!

donkeyክንፉ አሰፋ

"ደሳለኝ" ተብሎ ስለሚጠራው አህያ፤ በወያኔ ሜድያ የተተረከልን ታሪክ መሳጭ ነው። እነሱ ጫካ ውስጥ በነበሩበት ወቅት፣ አስገደ ገብረስላሴ በ45 ብር ገዝቶ ለወያኔ ማጓጓዣ ይሆን ዘንድ አበረከተ። ይህ "ደሳለኝ" የሚባለው አህያ ከባድ ጭነት እየተሸከመ ያገለግላቸው ነበር። በአንድ ወቅት በጦርነት ተሸነፉና ይዘውት የነነበረውን ስፍራ ለቅቀው ተበታተኑ። ከቀናት በኋላ አንዳንዶቹ ወደቀድሞ ምሽጋቸው ተመልሰው ለመምጣት እንኳን ሲቸገሩ ደሳለኝ ግን መንገዱን ሳይስት እዚያው ስፍራ ይጠብቃቸው ነበር። በመጨረሻም የአህዮች አለቃ ተባለና "ብፃይ" (ጓድ) የሚል የማዕርግ ሹመትን አገኘ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ