እሽሩሩ ኦነግ

ኦነግ

አንተነህ መርዕድ

የኦሮሞ ነፃነት ግንባር ለኦሮሞ ሕዝብ መብት የተነሳሁ ነኝ ቢልም፤ ባለፉ አርባ ዓመታት ለምን እንደቆመ ተግባሩ እያሳየን ነው። በተለይም በዚህ የለውጥ ጊዜ ኢትዮጵያን ወደየት ይዟት ሊሄድ እንደፈለገ በተግባር ያሳየን ስለሆነ፤ ዛሬ ሁሉም በሚገባ ያውቀዋል። ሁሉን አካታች የሆነው የኦሮሞ ሕዝብ በስሙ በሚካሄድ ወንጀል የአገሩ ሕልውና አደጋ ላይ እየወደቀ ከሌላው ወገኑ ጋርም በፍቅር የሚኖርበትን ሁኔታ እየተበላሸ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በቀለ ገርባ አብዷልና ዘመድ ካለው አማኑኤል ያስገቡት!

Bekele Gerba

አምባቸው ደጀኔ

አገራችን በየቀኑ መነጋገሪያ አጀንዳ አታጣም - በተለይ በዚህ ዘመንና በጣም በተለይ ደግሞ ባለፉት 12 ወራት። በነዚህ ሁለት ቀናት ደግሞ “አትርሱኝ” እያለ ያለው በቀለ ገርባ ነው።

ላለመረሳትና በሕዝብ አንደበት ዘወትር ለመወሳት እኮ በግድ ክፉና ጠማማ መሆን አያስፈልግም። ሰዎች እንዴት ነው እያሰቡ ያሉት? እንዴትስ ነው ያድጋሉ ሲባሉ እያነሱና እየኮሰመኑ የሚሄዱት? ምን ቢነካቸው ነው? አንድ ሰው ዕውቀትንና ጥበብን መጨመር ቢያቅተው ያለውን ይዞ መጓዝ እንዴት ይሳነዋል?

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ግንቦት ሰባት ከልምድህ …

Neamin Zeleke

ግርማ በላይ

አጤ ምኒልክ ከልምድዎ፤
አንዳንድ እያለ ቀረልዎ፤
አምናስ አለማያ ነበሩ፤
ዘንድሮን ወዴት ዋሉ?

ግንቦት ሰባት ከልምድህ፤
አንዳንድ እያለ ቀረልህ፤
አምናስ አሥመራ ነበርክ፤
ዘንድሮን ወዴት ዋልክ?

የኢትዮጵያ ሾተላይ ግዳይ መጣሉን ቀጥሏል። ልጆቿን ለሆነ ዓላማ ያሰባስባል፤ ከዚያም ቁም ነገር ሊያከናውኑ ሲሉ አንዳች ነገር ብን ያደርግባቸውና እያባላ ይበትናቸዋል - ደብተራዎች “አንደርብ” እንደሚሉት ዐይነት ነገር። አገሪቱ የሰብስብ ሣይሆን የበትን አለባት። ኢትዮጵያ ከምትወልዳቸው ልጆቿ ሙሉ በሙሉ ሳታያቸው በባህሉ መሠረት የጥቂቶቻችንን ጆሮ ቀንጠብ አድርገው ሰጥተዋት ካልበላችና የልጇን ጆሮ መብላቷን ነግረው ካላስደነገጧት በስተቀር የሾተላይ ዛሯ እንደ አገር የመቀጠሏን እድል እያጫጫው ነው። አሁንማ ሁሉ ነገር ኳስ አበደች ሆኗል። መንግሥት የለ፤ ሕዝብ የለ። ኦና ብቻ! ኦና አገር። ንብ-አልባ ቀፎ ሆነናል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

መንግሥት ሆይ! ቁስልንና መንሥኤን ለይ

Cause and Effect

ምሕረቱ ዘገዬ

ሁሉም ሰው በግልጽ የሚረዳው በሕክምናው ዓለም የሚተገበር አንድ አሠራር አለ። ይሄውም በአንድ ሕመም ውጫዊ የስቃይ ምልክቶችና ውጤታቸው ላይ ብቻ ከማተኮርና፤ የሕመም ስሜቶችን ብቻ እየተከታተሉ ስቃይን በማስታገሻ መድኃኒቶች ለተወሰነ ጊዜ ፋታ ከመስጠት በተጓዳኝ፤ የበሽታውን መንሥኤ ማጥናትና ሕመሙን ከሥር መሠረቱ አክሞ መፈወስ ተመራጭ የመሆኑ እውነታ ነው። ይህ አሠራር በጤናው ዘርፍ ብቻ የሚወሰን አይደለም።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ይድረስ በተለይ ለተፎካካሪ ፓርቲ አመራሮች

አቶ ዳውድ ኢብሳ፣ አቶ ለማ መገርሳ፣ ፕ/ር በየነ ጴጥሮስ፣ ፕ/ር መረራ ጉዲናና ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ
ነፃነት ዘለቀ (ከአዲስ አበባ)
በሰው የሚጠሉት ወይም እንደሚጠሉት የሚናገሩትን ራስ ሲያደርጉት የማያስጠላ ከሆነ የተሳከረ ስብዕና (MPD) ባለቤት የመሆን ችግር አለ ማለት ነውና፤ በቶሎ መታከም ያስፈልጋል። እኔ ለምሣሌ በወንድሜ ወይ በጓደኛዬ ላይ የማየውንና የምቃወመውን መጥፎ የመሰለኝን ምግባር እኔ ራሴ ባደርግና እንደነውር ባልቆጥር ትክክል አይደለሁም። ጨለማና ብርሃን ሕብረት እንደሌላቸው ሁሉ በአንድ ሰውነት ውስጥ ሁለትና ከዚያ በላይ ተቃራኒ ሰውነቶች ሊኖሩ አይችልም። እንደዚያ ያለ ችግር በፖለቲካው መስክ በጉልኅ እያስተዋልን ነው። ይህ አንቀጽ መግቢያዬ መሆኑ ነው። 
ሙሉውን አስነብበኝ ...

ድር ቢያብር አንበሳ ያስር

La Gare downtown luxury complex design, Addis Ababa

ዘ-ጌርሳም

ገና ስምንት ወር ብቻ ነው - ሕፃናት ተወልደው ቁመው የማይሄዱበት ዕድሜ፤ ከድምፅ በቀር ቃላት እንኳን አያወጡም። የኢትዮጵያ ሕዝብ ለዘመናት ተጭኖት ከነበረው የመከራና የግፍ አገዛዝ ቀንበር ራሱን ነፃ ለማድረግ፤ መራራና ፈታኝ መስዋእትነት ከፍሎ ለውጡን ለሚመሩለት ኃይሎች አስረክቧል። ይህ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የሚመራው መንግሥት በየቀኑ የሚያሳያቸውንና የሚያስመዘግባቸውን ለውጦች በአንክሮ ለሚከታተል ዕፁብ ድንቅ የሚያሰኝ ሆኖ ጥራቱና ፍጥነቱ ደግሞ የበለጠ ያስደምማል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

መፍትሔ የተራቡት የለውጡ ፈተናዎች

Dr. Abiy Ahmed

በቀለ ደገፋ፣ ኅዳር ፳፻፲፩ ዓ.ም.

በጠ/ሚ ዐቢይ የሚመራው የለውጥ ሥርዓት ወደሥልጣን ከመጣበት ዕለት አንስቶ እጅግ የሚያስደንቁና አንዳንዴም ለማመን የሚቸግሩ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል። በጥቂቱ ለማስታወስ - በወያኔ የማሰቃያ ቤቶች ተወርውረው የነበሩ ንጹሕንን ነፃ ማውጣት፣ በፖለቲካ አመለካከታቸው ሳቢያ ከአገር የተሰደዱ ኢትዮጵያውያንን ወደ ውድ አገራቸው እንዲመለሱ ማድረግ፣ አሸባሪ ሲባሉ የነበሩ የፖለቲካ ድርጅቶችን ወደ አገር ገብተው በነፃ እንዲንቀሳቀሱ ማድረግ፣ መቀመጫቸውን በውጭ ያደረጉ የመገናኛ ብዙኀን ሕዝብን በቀላሉ እንዲደርሱ እድል መስጠት፣ ትርጉም-አልባ የነበረውን የኢትዮ ኤርትራ ፀብ በእርቅ መፍታትና ብሎም በአፍሪካ ቀንድ የሰላም አየር እንዲነፍስ ማድረግ፣ ተለያይተው የነበሩ የቤተክርስቲያን አባቶችን በማስማማት የቅዱስ ሲኖዶሱን አንድነት መመለስ፤ እንዲሁም በባዕድ አገራት ለእስር ተዳርገው የነበሩ ኢትዮጵያውያንን አስፈትቶ ወደአገራቸው ማምጣት የሚሉት ይጠቀሳሉ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ አበባ ልገባ ነው!

Addis Ababa

ወለላዬ ከስዊድን

ኢትዮጵያ ልሄድ ነው። ይኼን እያሰብኩ እያለሁ እንባዬ ፊቴን ሞላው። እንደደረስኩ እቤት አልገባም። ተቀባዮቼን አስከትዬ ደብረ ሊባኖስ እሄዳለሁ። በናቴ መቃብር ላይ ሻማ ማብራትና አበባ ማስቀመጥ አለብኝ። በቦታው ላይ የማፈሰው እንባ ታየኝ። ከፊሉን አሁኑኑ ዘረገፍኩት። እናቴ ይኸው መጣሁ እናቴ ተቀበይኝ ... ያልቀበርኳት እናቴን ኀዘን በዛ ብቻ አልወጣውም፤ ግርግር ሳይኖር፣ ተው ባይ ሳይከተል፣ ብቻዬን ሌላ ቀን እመጣለሁ። ለናቴ የምነግራት ብዙ ነገር አለኝ። ሠንዬ እመለሳለሁ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አርበኞች ግንቦት 7 እና ቀጣይ ተግባሩ

Dr. Berhanu Nega and Mr. Andargachew Tsege

ስሜነህ ታምራት (ከስዊድን)

ዛሬ ኢትዮጵያችን በሰላማዊ ሽግግርና "በየአብሮነት ልዩነት" መርኅ በዴሞክራሲያዊ ግንባታ ላይ ትገኛለች። ስለሆነም ከዚህ ቀደም ያልተጠቀምንባቸውን አጋጣሚዎች ሁሉ በትምህርትነት ወስደን፤ ዛሬ የተፈጠረው ሁኔታ እንደትናንቱ እንዳያመልጠን ብዙ እጅግ በጣም ብዙ የሆነ ትዕግሥትና ብሔራዊ ትኩረት የምናደርግበት የለውጥ ነጋሪት እየተጎሰመ ያለበት ጊዜ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ