“በምርጫ ብቻ”

በምርጫ ብቻ

በሠለጠነ መንገድ ተወዳዳሪም፣ መራጭም፣ ታዛቢም፣ ደጋፊም እንሁን!

ኢትዮጵያ ዛሬ (ርዕሰ አንቀጽ) - የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ (ምርጫ 2013) ቦርድ የዘንድሮውን አገራዊ ምርጫ በተያዘለት ጊዜ ለማከናወን የሚያስችሉ ሥራዎችን እየሠራ ነው። እያጋጠሙት ያሉትን ችግሮች እያሳወቀና የመፍትሔ አቅጣጫ እያስቀመጠ እየተጓዘ መኾኑንም ቦርዱ በተከታታይ ከሚያወጣቸው መግለጫዎች ለመገንዘብ ይቻላል። ሁሉ ነገር አልጋ በአልጋ ባይኾንም ምርጫውን ለማካሔድ ጥረቱን ቀጥሏል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኢትዮጵያን አትንኩ የምንለው ለዚህ ነው

ኢትዮጵያን አትንኩ የምንለው ለዚህ ነው

ኢትዮጵያን መንካት ዋጋ የሚያስከፍል መኾኑን ማሳየት ተገቢ ነው

ኢትዮጵያ ዛሬ (ርዕሰ አንቀጽ) - የሱዳን አፈንጋጭ የጦር መኮንኖች በግብጽ ተገፋፍተው ወታደሮቻቸው የኢትዮጵያን ድንበር ጥሰው ከገቡ ሳምንታት ብቻ ሳይኾን፤ ወራት እየተቆጠሩ ነው። ኢትዮጵያ ፍጹም ለኾነው የሱዳን ስሕተት ትዕግሥትን በማስቀደም ነገሩን ከጦርነት መለስ ባለ ሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ይሻላል በማለት በዚሁ አኳያ እየተንቀሳቀሰች ነው። ይህም ቢኾን ግን ከሱዳን ቀና ምላሽ ባለመገኘቱ የኢትዮጵያን ድንበር የተራመዱቱ የሱዳን ታጣቂዎች ከኢትዮጵያ ግዛት ከመውጣት ይልቅ ቆይታችንን እናራዝማለን በሚል አንዳንድ ግንባታዎችን እስከማካሔድ ደርሰዋል። ይህ ድርጊታቸው ደግሞ ነገሩን ይበልጥ እያከረረው በመኾኑ፤ በአካባቢው ጦርነት ይነሳል የሚል ሥጋት መፍጠሩ አልቀረም።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ሕገወጥ ተግባርን በሕገወጥ መንገድ ለማከም መሞከር

ሕገወጥ ዘይት መያዙ ብቻ ሳይሆን የተያዘውን ዘይት በሕገወጥ መንገድ እንዲሠራጭ ማድረጉም ሌላ ሕገወጥነት ነው

የዘይቱ መዘዝ ገና ብዙ ነገር ያሳየናል

ኢትዮጵያ ዛሬ (ርዕሰ አንቀጽ) - አገርን እንደ አገር ለማስቀጠልና የተሻለች ኢትዮጵያን ለቀጣይ ትውልድ ለማስረከብ እጅግ በርካታ ሥራዎች ከፊታችን ይጠብቁናል። እድገትን ቀጣይ ለማድረግና ለዜጐች ምቹ የኾነች አገር ለመፍጠር ከሚያስፈልጉ ወሳኝ ጉዳዮች መካከል ለሕግ መገዛት፣ በሕግ አግባብ መጓዝና አድሎ የሌለው የፍትሕ ሥርዓትን ማስፈን ቁልፍ ጉዳዮ ናቸው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የዘንድሮዋን ዳግማይ ትንሣኤ በጨረፍታ

ዳግም ትንሣኤ

ለዳግማይ ትንሣኤ እሁድ የተለየ አዋጅ የወጣ ይመስል ነበር

(ማህደር ዳ. | ኢዛ) ባለፈው እሁድ ሚያዝያ 18 ቀን 2012 ዓ.ም. ነው። በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ ዳግማይ ትንሣኤ ነበር። በዚህ ዕለት ዘመድ አዝማድ የሚገናኝበት፤ አክፋይ ይዞ እንኳን አደረሳችሁ፣ እንኳን አደረሰን የሚባባልበት ቀን ነው። እንዲህ ያለውን የእንኳን አደረሳችሁ መልእክትና መልካም ምኞት ለመግለጽ አገር አቆራርጠው ወላጆችና አማች ቤት የመሔዱ ልምድ በአብዛኛው የአገሪቱ ማኅበረሰብ ዘንድ የሚከናወንበት ነው። የቆየ ወግና ልማዳችን ኾኖ ለዘመናት እየኖርነው እስካሁን ደርሰናል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ሕጋዊነትን እናስከብራለን ተብሎ፤ እጥረትና ኢኮኖሚያዊ ክስረትን እንዳያመጣ

ታሽጓል

በማሸግ የሚካሔደው የሕግ ማስከበር ሥራ የበለጠ ውጤታማ ለማድረግ …

ኢትዮጵያ ዛሬ - ዓለም የበረታ ጭንቅ ውስጥ ገብታለች። ዘር፣ ቀለም፣ ሃይማኖት ሳይለይ በአንድ ቫይረስ በየዕለቱ የሞት መርዶ እየተነገረባ ነው። በሀብት መጠናቸው የፈረጠሙ፣ በዴሞክራሲ እርምጃቸው የሚቆለጳጰሱ የዓለማችን ልዕለ ኃያላን አገሮች ሁሉ በዚህ ወረርሽኝ እያለቀሱ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አድዋ ሕያው ነው! (አንተነህ እምሩ)

እቴጌ ጣይቱና ዳግማዊ ምኒልክ

አድዋ የኛ ብቻ ሳይኾን የአፍሪካውንና የመላው ጥቁር ሕዝቦች ድል ነው!

ጀግኞች አባቶቻችን ባደረጉት ተጋድሎ ኢትዮጵያ በነፃነት ኮርታ ኖራለች። አፍሪካውያን ወንድሞቻችንና በቅኝ አገዛዝ ቀንበር የነበሩ የዓለም አገራት የነፃነት ተስፋ የሰነቁትና የቅኝ አገዛዝን ፍጻሜ ትግል የጀመሩት በአባቶቻችን አብሪ ድል ብርሃን አግኝተው ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ጠ/ሚ ዐቢይን በአጼ ምኒልክ ግቢ ስለመጎብኘቴ (ፕሮፌሰር ፍቅሬ ቶሎሳ ጂግሳ)

Prof. Fikre Tolossa & PM Dr. Abiy Ahmed

ከዶክተር ዐቢይ ጋራ በቢሮአቸው ውስጥ ለአንድ ሰዓት ተኩል ያህል ስለ ኢትዮጵያ ወቅታዊ ጉዳዮዎች ተነጋገርን

(ፕሮፌሰር ፍቅሬ ቶሎሳ ጂግሳ) በሐምሌ ወር መጨረሻ ይመስለኛል። ከዐምስት ወራት በፊት። በምኒልክ ቤተመንግሥት አዲስ በገነቡት ቢሮአቸው ውስጥ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይን አገኘኋቸው። ገና እንደአገኙኝ አቅፈው ተቀብሉኝ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የብልጽግና ፓርቲ ረቂቅ መተዳደሪያ ደንብ ማርሽ ቀያሪ አንቀጾች

Critic on Prosperity party regulations

"አጋሮች ድሮውንም ከ4 ኪሎና ከመቀሌ በቀጭን ሽቦ በምትተላለፍ ትእዛዝ ጉዳያቸውን ሲፈጽሙና ሲያስፈጽሙ ስለሰነበቱ፣ አዲስ ነገር እንደማይሆንባቸውና አግኝተው ያጡት መብት ብዙም ፍንትው ብሎ ስለማይታያቸው፤ አዲሱን የድርጅታዊ አወቃቀር ሊቀበሉት ይችላሉ" ራሚደስ

በAddis Standard ድረገጽ የተለጠፈው የብልጽግና ፓርቲ ረቂቅ መተዳደሪያ ደንብ ያቃጨለው ደውል ቀላል የማይባልና ላለፉት ሦስት አሥርት ዓመታት ገደማ ኢሕአዴጋዊው የኢትዮጵያ አገረ መንግሥት ግንባታ ፕሮጀክት ሥር ነቀል ለውጥ የሚያስከትል መኾኑን ያበሰረ ወይንም ያረዳ ነው። ይህ ረቂቅ በኢሕአዴግ እኅት ድርጅቶችና በግንባሩ ጠቅላላ ጉባዔ ጸድቆ ወደ ተግባር መግባት ከቻለ የኢትዮጵያ ፌደራሊዝም ቢያንስ በወረቀት ላይ ሰፍሮ ከሚገኘው ያልተማከለ አስተዳደር ወደ ኢሠፓ መሰል የተማከለ አስተዳደር አስፈንጥሮ እንደሚያስገባው እሙን ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ፓሪስ ላይ አባቴን አገኘሁት

La tour eiffel, Paris

ከዘንድሮ የበጋ እረፍቴ ውስጥ አስሩን ቀን ፈረንሳይ ለማሳለፍ አስቤ ወደ ፓሪስ አቀናሁ

ወለላዬ ከስዊድን

ተማሪዎች ሁሉ ክፍል ተመድበው ትምህርት በጀመሩበት የጥቅምት ወር አጋማሽ ላይ መርዕድ አዝማች ስብስቴ ነጋሲ ት/ቤት ተገኘሁ። ትምህርት ቤቱ እንደ ስብስቴ ረዥም ዕድሜ እንዳለው ይነገርለታል። ከዛ ት/ቤት ስም በስተቀር ለሌላ ሰው ወይም ተቋም ስም ሲወጣ ሰምቼ አላውቅም። ስሙ እንዳይረሳ ያደረገው የት/ቤቱ ስምና ሩቅ ዘመንን ለመግለጽ “ኡ ... የስብስቴ ጊዜ እኮ ነው …" የሚባለው አባባል ይመስለኛል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ብሔር፣ መንግሥትና ሕዝብ - የፖለቲካ ግብ ማሳለጫ ግንዛቤነታቸው

"የአዋሳ ከተማ፣ የሐረር ከተማ፣ የድሬዳዋ ከተማ፣ የአዲስ አበባ ከተማ፣ ሌሎችም ትልልቅ ከተሞችና የንግድ ማዕከሎች፤ የመተላለቂያ ቦታዎች ከመሆን አይድኑም"

አንዱ ዓለም ተፈራ

አገራችን አሁን ያለችበት የፖለቲካ ቀውስ፤ ሥር መነሻ አለው። ይህ ቀውስ ትክክለኛ መፍትሔ እንዲያገኝና የተጀመረው የለውጥ ሂደት ግቡን እንዲመታ፤ መሠረታዊ የሆኑ የሕብረተሰባችን ግንዛቤዎቻችን ሊለውጡና፤ በአመራሩም በኩል ተገቢ የፖለቲካ እርምጃዎች ሊወሰዱ ይገባቸዋል። ያለው ሐቅ፤ ላለፉት ሃያ ሰባት ዓመታት በትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር (ሕወሓት) መንግሥት ሲካሄድ የነበረው ዕልቂት፤ አሁንም በየቦታው ቀጥሎ መጧጧፉ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ