ጥብቅ ማሳሰቢያ ለጠ/ሚኒስትር ዐቢይ - እኔም በሀገሬ ያገባኛል!
ምሕረት ዘገዬ
መረጃ አይናቅም። መረጃ ሁሉ በግርድፉ እንደ እውነት አይወሰድም። መረጃዎች እንደየምንጫቸው ሰውን/ተቋምን ለማሳሳት፣ ለማደናገር፣ ለማስፈራራት፣ ለማስጠንቀቅ፣ ለማሳወቅ፣ ወዘተ ... ይለቀቃሉ። ጥንቃቄ ማድረግ የሚያሻው መረጃ ተጠቃሚው ወገን ነው።
ጠ/ሚ ዐቢይ ሥራው የተቃና ይሆን ዘንድ፣ እኛም ዜጎች የሚታየንን ባሉን ማስንተፈሻዎች እንጠቁማለን፤ ሰሚ ካገኘን እሰዬው። ሰሚ ባናገኝ ቢያንስ ከኅሊና ወቀሳ እንድናለን። የሚነገሩ ሁሉ እውነት ሊሆኑ እንደማይችሉ ሁሉ፤ የሚነገሩ ሁሉ ሐሰት ሊሆኑም አይችሉም። የአንድ መሪም ሆነ ጉዳዩ የሚመለከተው ወገን ዋና ኃላፊነት እውነቱን ከውሸቱ አበጥሮ የመለየት ትልቅ ተግባር ነው።
ሙሉውን አስነብበኝ ...



