ቆነጃጅት፣ ወይንና ቅኔ
አበራ ለማ
ይድረስ ለሥነኪን ተጠባቢው አለማየሁ ታዬ - ታለህበት
ይህች ሂሣዊ ንባብ አከል ማስታወሻዬ ትድረስህ። እንደ ተጋባዥ የሥነ ግጥም የኔታ ሁኜ፣ አንተ ደግሞ የ”ፍካታ የሥነ-ጽሑፍ ክበብ” ታሊባን* ሁነህ የዛሬ አሥራ ምናምን ዓመታት በፊት እንደተዋወቅን ከላክልኝ መልዕክት ተረድቻለሁ። የዘሩት በቅሎ፣ አሽቶ፣ ፍሬውም ጎምርቶና በስሎ ከማየት በላይ ላንድ ገበሬ ምን የሚያስደስተው ፀጋ አለ? የኔና ያንተም ትውውቅና ቁርኝት በዚህ ሊመሰል ታድሏልና እሰየው ነው።
ደገኛው ወዳጃችንና ሞክሼህ ዓለማየሁ ዲባባ ምስጋና ይግባውና (ከምድረ ስዊድን)፣ በሱ በኩል የላክልኝን በረከቶችህን አቀብሎኝ፣ በናፍቆት እንደተገኘ የቡሄ ጥቢኛ እያገላበጥኩ ስኮመኩመው ሰንብቻለሁ። ... (ሙሉውን ጽሑፍ በፒ.ዲ.ኤፍ. አስነብበኝ!)