የፕሮፌሰር መስፍን ሥርዓተ ቀብር ነገ ይፈጸማል
ከቀብር ሥነ ሥርዓቱ በፊት የሻማ ማብራትና የሽኝት ፕሮግራም ይካሔዳል
ኢዛ (ሰኞ መስከረም ፳፭ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. October 5, 2020)፦ የፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም የቀብር ሥነ ሥርዓት ነገ ማክሰኞ መስከረም 26 ቀን 2013 ዓ.ም. በቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ቤተ ክርስቲያን ይፈጸማል።
የቀብር ሥርዓቱን ለማስፈጸም የተቋቋመው ኮሚቴ እንዳስታወቀው፤ ነገ የቀብር ሥርዓቱ ከመፈጸሙ በፊት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ልደት አዳራሽ የሽኝት ፕሮግራም ይካሔዳል።
ዛሬ ምሽት ላይ ደግሞ በመኖሪያ ቤታቸው የሻማ ማብራት ፕሮግራም እንደሚኖርም ተጠቅሷል።
የልደት አዳራሹ ፕሮግራም ልጆቻቸው እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት የሚፈጸም እንደሚኾን ታውቋል። (ኢዛ)