PM Dr. Abiy Ahmed

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ

ሁለቱ ባለሥልጣናት የተሾሙት በሚኒስትር ማዕረግ ነው

ኢዛ (ዓርብ ኅዳር ፲፱ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. November 29, 2019)፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ለሦስት የመንግሥት ኃላፊዎች ሹመት ሠጡ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሹሙት የሠጡዋቸው አቶ አሕመድ ቱሳ፣ ዶ/ር ዓለሙ ስሜና አቶ አወሉ አብዱ ናቸው።

በሹመቱ መሠረት አቶ አሕመድ የብረታ ብረትና ኢንጂንየሪንግ ኮርፖሬሽን የኢንዱስትሪ ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይፌክተር ኾነው ሲሾሙ፣ ዶ/ር ዓለሙ ስሜ ደግሞ በሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል አስተባባሪ በመኾን መሾማቸው ታውቋል።

ትናንት ኅዳር 18 ቀን 2012 ዓ.ም. በጠቅላይ ሚኒስትሩ የተሾሙት ሦስተኛው ሰው፣ አቶ አወሉ አብዲ ሲሆኑ፣ በሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል የሕዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ኃላፊ ኾነው እንዲሠሩ ነው።

ተሿሚዎቹ ከዚህ ቀደም አገልግለዋል?

ከዛሬ ተሿሚዎች ውስጥ አንዱ አቶ አሕመድ ቱሳ በተለያዩ የመንግሥት የኃላፊነት ቦታዎች ተመድበው ረዥም ጊዜ ካገለገሉ የመንግሥት ባለሥልጣናት መካከል አንዱ ናቸው።

ከዚህ ቀደም ለዓመታት ካገለገሉባቸው የኃላፊነት ቦታዎች ውስጥ የንግድ ሚኒስትር ዴኤታ ኾነው ማገልገላቸው ይጠቀሳል። የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክ ኢንተርፕራይዝ ዋና ዳይሬክተር በመኾንም ሠርተዋል።

ዶ/ር ዓለሙ ስሜም የኢንዱስትሪ ሚኒስትር ዴኤታ እንደነበሩ የሚታወስ ሲሆን፣ በተመሳሳይ በመንግሥት የተለያዩ የኃላፊነት ቦታዎች ለበርካታ ዓመታት ሠርተዋል። በክልል ደረጃም የኦሮሚያ የውኃ ማዕድንና ኢነርጂ ቢሮ ኃላፊ በመኾን መሥራታቸውም ይታወሳል። በፓርቲ አገልግሎት ደግሞ፣ የኦዴፓ ማዕከላዊ ኮሚቴ ኃላፊ በመኾን ሲያገለግሉ ቆይተዋል።

አቶ አወሉ አብዲሳ በኦሮሚያ ክልል በተለያዩ የኃላፊነት ቦታዎች ላይ የቆዩ ሲሆን፣ በተለይ የኦሮሚያ ክልል የሥራ እድል ፈጠራና የምብግ ዋስትና ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር በመኾን ማገልገላቸው ይጠቅሳል።

ሦስቱም ተሿሚዎች የቀድሞ ኦሕዴድና የአሁኑ ኦዴፓ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት እንደኾኑም ይታወቃል። (ኢዛ)

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ