ፖምፒዮ አዲስ አበባ ናቸው
ዛሬ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር ይገናኛሉ
ኢዛ (ማክሰኞ የካቲት ፲ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. February 18, 2020)፦ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማይክ ፖምፒዮ ትናንት ምሽት አዲስ አበባ ገብተዋል። በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ የተቀበሏቸው አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ናቸው።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ዛሬ ከኢትዮጵያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ጋር ይመክራሉ። ፓምፒዮ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድና ከፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ጋርም ይወያያሉ ተብሎ ይጠበቃል። (ኢዛ)