Gonder Airport

ጎንደር ዐፄ ቴዎድሮስ ኤርፖርት

ምክንያቱ በባሕር ዳር እና በጎንደር የተከሰተውን የሮኬት ጥቃት ነው

ኢዛ (ቅዳሜ ኅዳር ፭ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. November 14, 2020)፦ በባሕር ዳር እና በጎንደር የተከሰቱትን ፍንዳታዎች ተከትሎ ጥቃቱ በደረሰ ማግስት ወደ ሰሜን ኢትዮጵያ ይደረጉ የነበሩ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በረራዎች እንዲሰረዙ ተደርገዋል። የሮኬት ጥቃቱ የፈጸመው የሕወሓት ጁንታ ቡድን ትናንት ከምሽቱ አምስት ሰዓት ላይ ነበር።

በአደጋው ማግስት ዛሬ ቅዳሜ ኅዳር 5 ቀን 2013 ዓ.ም. ወደ ጎንደር፣ ባሕር ዳር፣ ላሊበላ ከተሞች የተያዙ በረራዎች በሙሉ ላልተወሰን ጊዜ እንዲቋረጡ በመደረጉ፤ ወደ እነዚህ ከተሞች በረራ የነበራቸው ተጓዦች ከበረራቸው ተስተጓጉለዋል።

እነዚህ በረራዎች መሰረዛቸውንም አየር መንገዱ ያስታወቀ ሲሆን፤ በዕለቱ በረራ ለነበራቸው ተጓዦች ይህንኑ ለማስታወቅ ተገድዷል። (ኢዛ)

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ