ፈንጂዎች

ከመቀሌ ወደ አዲስ አበባ በመጓጓዝ ላይ የነበሩትና በወልዲያ ጉምሩክ ኬላ የተያዙት 207 ፈንጂዎች

አሽከርካሪው በፖሊስ ቁጥጥር ሥር ውሏል

ኢዛ (ረቡዕ የካቲት ፲ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. February 17, 2021)፦ መዳረሻውን አዲስ አበባ ያደረገና ከመቀሌ የተጫኑ 207 ፈንጂዎች በመጓጓዝ ላይ እንዳለ ወልዲያ በሚገኝ ጉምሩክ ኬላ ላይ ተያዘ።

እያንዳንዳቸው ዘጠኝ ፈንጂዎችን የያዙ 23 ካርቶኖች የተያዙት በወልዲያ ጉምሩክ ኬላ ላይ እንደኾነ ተገልጿል።

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንዳመለከተው፤ ከመቀሌ ወደ አዲስ አበባ ፈንጂዎቹን ጭኖ ሲጓጓዝ የነበረው አሽከርካሪ በፖሊስ ቁጥጥር ሥር ውሏል። (ኢዛ)

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ