የኤርትራ ወታደሮች እየወጡ ነው
የኤርትራ ሰንደቅ ዓላማ
ከትግራይ አካባቢዎች ተንቀሳቅሶ ወደ ኢትዮ-ኤርትራ ድንበር መመለስ መጀመሩ ተዘገበ
ኢዛ (ሐሙስ ሰኔ ፲ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. June 17, 2021)፦ የሕወሓት ቡድን በኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ላይ የፈጸመውን ጥቃት ተከትሎ በተቀሰቀሰው ጦርነት ወደ ኢትዮጵያ ገብቶ የነበረው የኤርትራ መከላከያ ሠራዊት ከኢትዮጵያ ግዛት መውጣት መጀመሩ ተገለጸ።
የኤርትራ መከላከያ ሠራዊት ከነበረበት ከተለያዩ የትግራይ አካባቢዎች ተንቀሳቅሶ ወደ ኢትዮ-ኤርትራ ድንበር መመለስ ስለመጀመሩ የኤርትራ ፕሬስ ምንጮች ጠቅሶ ዘግቧል። (ኢዛ)



