የሰብአዊ መብት ኮሚሽን ምክትል ዋና ኮሚሽነር ተሰየመለት
ዶ/ር ዳንኤል በቀለ (የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮምሽን ዋና ኮሚሽነር)
የሦስት የዘርፍ ኮሚሽኖችም ሹመት ጸደቀ
ኢዛ (ዓርብ ሰኔ ፲፰ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. June 25, 2021)፦ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽንን (ኢሰመኮን) በምክትል ኮሚሽነርነት እና በተለያዩ ዘርፎች ኮሚሽን ኾነው የሚያገለግሉ ተሿሚዎች ሹመት ዛሬ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጸደቀ።
በዶ/ር ዳንኤል በቀለ የሚመራውን የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽንን በተለያዩ የኃላፊነት ደረጃዎች እንዲመሩ ዛሬ ዓርብ ሰኔ 18 ቀን 2013 ዓ.ም. ሹመታቸው ከጸደቀላቸው ውስጥ ወ/ሮ ራኬብ መለስ የኮሚሽኑ ምክትል ዋና ኮሚሽነር ኾነዋል።
ወ/ት እርግብ ገብረሐዋርያ ደግሞ የአካል ጉዳታኞች እና አረጋውን መብቶች ኮሚሽነር ኾነው እንዲያገለግሉ ተሹመዋል።
የኮሚሽኑ የፖለቲካ መብቶች ጉዳዮች ኮሚሽነር እንዲኾኑ የተሾሙት ዶ/ር አብዲ ጅብሪል ናቸው። የኮሚሽኑ የሴቶች እና ሕፃናት መብቶች ጉዳዮች ኮሚሽነር ኾነው እንዲያገለግሉ የተሾሙት ደግሞ ወ/ሮ መስከረም ገስጥ ናቸው። (ኢዛ)



