የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን በ1147 አመራር እና አባላት ላይ እርምጃ መውሰዱ ተገለጸ

Commissioner Getu Argaw

በምርጫው የጸጥታ ችግሮች እንዳይከሰቱ በልዩ ትኩረት እየሠራ እንደሚገኝ አስታወቀ

ኢዛ (ሐሙስ መጋቢት ፴ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. April 8, 2021)፦ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን፤ ባለፉት ዘጠኝ ወራት 1,147 የሚኾኑ የፖሊስ አመራር እና አባላት ላይ ቀላል እና ከባድ የዲሲፕሊን እርምጃ መውሰዱ ተገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ዋና ሥራ አስፈጻሚ ከኃላፊነታቸው አለመነሳታቸውን አስታወቁ

Mulu Nega

ዶ/ር ሙሉ ነጋ በክልሉ ያሉ ወጣት አመራሮችን አላግባብ ከኃላፊነታቸው አንስተዋል ተብለው ይታማሉ

ኢዛ (ረቡዕ መጋቢት ፳፱ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. April 7, 2021)፦ በፌዴሬሽን ምክር ቤት ውሳኔና በሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ የጸደቀውን የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር በዋና ሥራ አስፈጻሚነት እየመሩ ያሉት ዶ/ር ሙሉ ነጋ ከኃላፊነታቸው መነሳታቸው በማኅበራዊ ትስስር ገጾች የተነገረ ቢኾንም፤ እሳቸው ግን በሥራ ላይ እንደሚገኙና ከኃላፊነታቸው ስለመነሳታቸው እንደማያውቁ መግለጻቸው ተነገረ። ተሰማ። ዶ/ር ሙሉ በክልሉ ያሉ ወጣት አመራሮችን ከኃላፊነታቸው አንስተዋል ተብለው ይታማሉ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የኦሮሚያ ክልል ኦነግ ሸኔን በ15 ቀን እደመስሳለሁ አለ

Getachew Balcha

ኦነግ ሸኔን ከመደምሰስ ባሻገር ከዘመቻው ጋር ያልተባበሩ እና ኃላፊነታቸውን በአግባቡ ያልተወጡ የመንግሥት አመራሮችም ከመጠየቅ አያመልጡም ተብሏል

ኢዛ (ረቡዕ መጋቢት ፳፱ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. April 7, 2021)፦ ዛሬ ረቡዕ መጋቢት 29 ቀን 2013 ዓ.ም. ከኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት የተሰማው አንድ መረጃ በብርቱ የሚጠበቅ፤ ምናልባትም አገሪቱን በአሁኑ ሰዓት ያለችበትን ያለመረጋጋትና ዘር ተኮር ጭፍጨፋን ያስቀራል ተብሎ የተገመተ ነው። ይህ ከክልሉ መንግሥት የተሰማው ዜና በአሁኑ ወቅት በጅምላ ጭፍጨፋ ቀዳሚ ተጠያቂ የኾነውን የኦነግ ሸኔ በአሥራ አምስት ቀን ውስጥ ልክ አስገባዋለሁ ማለቱ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በዝግ ችሎት ይሰማ የተባለው ምስክርነት ውድቅ ኾነ

Jawar Mohammed (L), Bekele Gerba (R)

በእነ አቶ ጃዋር ላይ የዓቃቤ ሕግ ምስክሮች በግልጽ ችሎት ምስክርነታቸው ይሰማ ተብሎ ብይን ተሰጠ

ኢዛ (ማክሰኞ መጋቢት ፳፰ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. April 6, 2021)፦ ዓቃቤ ሕግ በእነ ጃዋር መሐመድ ላይ በዝግ ችሎት ላሰማ ያለው የምስክር የአሰማም ሒደት ጥያቄ ውድቅ በማድረግ፤ ምስክሮቹ በግልጽ ችሎት ምስክርነታቸውን እንዲሰጡ ብይን ተሰጠ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኢትዮጵያ በኮቪድ 19 ጽኑ ሕሙማን ቁጥር የመጀመሪያውን ደረጃ ይዛለች

ዶ/ር ሚዛን ኪሮስ

ቫይረሱ በአሁኑ ጊዜ ባለባቸው ሰዎች ቁጥር ከአፍሪካ ቀዳሚ ናት

ኢዛ (ማክሰኞ መጋቢት ፳፰ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. April 6, 2021)፦ በኢትዮጵያ የኮቪድ 19 ወረርሽኝ በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ ከመምጣቱ ጋር ተያይዞ አሳሳቢ በሚባልበት በዚህ ሰዓት፤ በጽኑ ሕሙማን ቁጥር ከአፍሪካ የመጀመሪያውን ደረጃ ልትይዝ መቻሏ ተገለጸ። በአሁኑ ሰዓት ኮሮና ቫይረስ ባለባቸው ሰዎች ቁጥርም፤ ከአፍሪካ ቀዳሚነቱን እንደያዘች ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የብሮድካስት ባለሥልጣን አዳዲስ ዋናና ምክትል ዳይሬክተሮች ተሾሙ

Yonatan Tesfaye

አንዱ ተሿሚ ዮናታን ተስፋዬ ነው

ኢዛ (ሰኞ መጋቢት ፳፯ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. April 5, 2021)፦ በቅርቡ ኃላፊነታቸውን በገዛ ፍቃዳቸው በለቀቁት በቀድሞ የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ምትክ እና በሹመት ወደ ሌላ መሥሪያ ቤት በሔዱት ምክትል ዋና ዳይሬክተሮች ምትክ አዳዲስ ኃላፊዎች ተሾሙ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የዘር ተኮር ጥቃቱ አምስት ፓርቲዎችን በጋራ አቋማቸውን እንዲገልጹ አድርጓል

የዘር ማጥፋት በምዕራብ ወለጋ ዞን ባቦ ጋምቤል ወረዳ ቦኔ ቀበሌ

መንግሥት ድርጊቱን እንዲያስቆም አሳስበዋል
እጃቸው ያለበት ባለሥልጣናትም ለሕግ እንዲቀርቡ ጠይቀዋል
“አፋቸውን የከፈቱ ጅቦች ትንንሽ አይጦችን በመላክ ኢትዮጵያን ለመዋጥ እየጣሩ ነው” ጠ/ሚ/ር ዐቢይ አሕመድ

ኢዛ (እሁድ መጋቢት ፳፮ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. April 4, 2021)፦ ማንነትን መሠረት ያደረገ ጥቃትን በመቃወም እና ድርጊቱ እንዲቆም የተፎካካሪ ፓርቲዎች በጋራ አቋማቸውን ያንጸባረቁበትን መግለጫ ትናንት አውጥተዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አቢሲኒያ ባንክ ካፒታል አሥር ቢሊዮን ብር እንዲኾን ወሰነ

Bank of Abyssinia

ከብሔራዊ ባንክ ጫና ነበረበት

ኢዛ (ሐሙስ መጋቢት ፳፫ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. April 1, 2021)፦ ከግል ባንኮች ውስጥ ቀድመው ከተቋቋሙ ባንኮች መካከል አንዱ የኾነው አቢሲኒያ ባንክ፤ በዛሬው ዕለት ባካሔደው ድንገተኛ አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባዔ፤ የባንኩን ካፒታል አሥር ቢሊዮን ብር ለማድረግ ወሰነ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ያላባራው ግድያ በኦሮሚያ ከሃያ በላይ ሰዎችን ነፍስ ቀጠፈ

Gembel, West Wellega, Ethiopia

በምዕራብ ወለጋው ጥቃት ጅምላ ጭፍጨፋ መኾኑን ከጥቃቱ የተረፉት ገለጹ

ኢዛ (ረቡዕ መጋቢት ፳፪ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. March 31, 2021)፦ በምዕራብ ወለጋ ዞን ባቦ ጋምቤል ወረዳ ቦኔ በሚል በምትታወቅ ቀበሌ ውስጥ በርካታ ሰዎች መገደላቸውን እና መቁሰላቸው ተገለጸ። ድርጊቱ ዘር ተኮር የኾነ የጅምላ ጭፍጨፋ (ዘር ማጥፋት) ነው ሲሉ ከጥቃቱ የተረፉ የአማራ ተወላጆች ገለጹ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በትግራይ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ማሻሻያ ተደረገበት

Mekele

ከምሽቱ አንድ ሰዓት የነበረው የሰዓት እላፊ ገደብ ወደ ሁለት ሰዓት ተራዘመ

ኢዛ (ረቡዕ መጋቢት ፳፪ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. March 31, 2021)፦ ላለፉት አራት ወራት በትግራይ ክልል ተፈጻሚ እየኾነ ያለው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የተደነገገው የሰዓት እላፊ ገደብ ማሻሻያ እንደተደረገበት ተገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ