ለአገር መከላከያ የሚሰጠው ድጋፍ ቀጥሏል

Muferiat Kamil

ድጋፉን በማዕከል ለማድረግ ኮሚቴ ተዋቅሯል

ኢዛ (ረቡዕ ኅዳር ፪ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. November 11, 2020)፦ ለመከላከያ ሠራዊት እየተደረገ ያለውን ድጋፍ ለማስተናገድ የተለያዩ የፌደራል ተቋማትን ያሳተፈ ብሔራዊ ኮሚቴ መቋቋሙንና የመከላከያ ሠራዊት እያካሔደ ያለውን ሕግን የማስከበር ሥራ በመደገፍ ሕብረተሰቡ ፍቅርና ክብሩን እየገለጸ እንደሚገኝ የሰላም ሚኒስትሯ ወ/ሮ ሙፈሪያት ካሚል ገለጹ። ሚኒስትሯ ይህንን የገለጹት በወቅታዊ አገራዊ ጉዳይ በተዘጋጀ መድረክ ላይ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ነፃ በወጡ የትግራይ አካባቢዎች ጊዜያዊ አስተዳደር እንደሚቋቋም ተገለጸ

Kenea Yadeta, defence minister

ሕወሓት በአምስት ጉዳዮች ላይ አተኩሮ ሐሰተኛ መረጃዎችን እያሠራጨ ነው

ኢዛ (ረቡዕ ኅዳር ፪ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. November 11, 2020)፦ ከጥፋት ኃይሉ ነፃ በወጡ የትግራይ ክልል አካባቢዎች ጊዜያዊ አስተዳደር የሚቋቋምለቸው መኾኑን የመከላከያ ሚኒስትሩ ዶክተር ቀነአ ያደታ ዛሬ ረቡዕ ኅዳር 2 ቀን 2013 ዓ.ም. በሰጡት መግለጫ አስታወቁ። ቡድኑ በአምስት ጉዳዮች ላይ አተኩሮ ሐሰተኛ መረጃዎችን እያሠራጨ መኾኑንም ገልጸዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የአማራ ብልጽግና ፓርቲ አዲስ የጽሕፈት ቤት ኃላፊ ሾመ

አቶ አብርሃም አለኸኝ እና አቶ አገኘው ተሻገር

አቶ አብርሃም አለኸኝ አዲሱ ተሿሚ ኾነዋል

ኢዛ (ረቡዕ ኅዳር ፪ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. November 11, 2020)፦ የአማራ ክልል የብልጽግና ፓርቲ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ የነበሩት አቶ አገኘው ተሻገር የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኾነው መሾማቸውን ተከትሎ፤ የክልሉን የብልጽግና ጽሕፈት ቤት እንዲመሩ አቶ አብርሃም አለኸኝ ተሾሙ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በአዲስ አበባ ቦንብ ፈንድቶ አንድ ግለሰብ ላይ ጉዳት ደረሰ

የአዲስ አበባ ታክሲዎች

የሕገወጡ ሕወሓት ቡድን ተላላኪዎች በመዲናዋ የጥፋት ተግባር ለመፈጸም ያዛጋጇቸው የጦር መሣሪዎች ተይዘዋል

ኢዛ (ረቡዕ ኅዳር ፪ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. November 11, 2020)፦ በአዲስ አበባ አድዋ ድልድይ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ዛሬ ጠዋት ቦምብ ፈንድቶ በአንድ ግለሰብ ላይ ጉዳት መድረሱን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኢትዮጵያ በታሪኳ እንደ ሕወሓት ዐይነት አረመኔ ገጥሟት እንደማያውቅ አቶ ደመቀ መኮንን ገለጹ

Demeke Mekonen

ከሃዲ ቡድኑ ማንነት ላይ ያነጣጠረውን ጥቃት ቀጥሏል አሉ

ኢዛ (ረቡዕ ኅዳር ፪ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. November 11, 2020)፦ ዛሬ በይፋ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትርነት ሥራቸውን የጀመሩት አቶ ደመቀ መኮንን በምድር ላይ የመጨረሻ የክፋት መገለጫዎችን ከመፈጸም ወደኋላ የማይመለሰው ቡድን፤ በየክልሉ ጽንፈኞችን እያስተባበረ በማንነት ላይ ያነጣጠረ ጭፍጨፋ መፈጸሙን ቀጥሎበታል አሉ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ሕወሕት ታጣቂዎቹን የኤርትራ መከላከያ መለዮ በማልበስ “ኤርትራ ወራናለች” እያለ ነው

M. Gen. Mohammed Tessema

መለዮውን ያመረተው በአልመዳ ጨርቃ ጨርቅ ነው

ኢዛ (ረቡዕ ኅዳር ፪ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. November 11, 2020)፦ ሕወሓት የኤርትራ መከላከያ ሠራዊትን መለዮ በአልመዳ ጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካ በማምረትና ላደራጃቸው ታጣቂዎች በማልበስ፤ “ኤርትራ ወራናለች” በማለት ሕዝቡን እያደናገረ መኾኑን የመከላከያ ሠራዊት የኢንዶክትሪኔሽን ዋና ዳይሬክተር ሜጀር ጄኔራል መሐመድ ተሰማ ዛሬ አስታወቁ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ሕግ እስኪከበር የአየር ጥቃቱ ያለከልካይ እንደሚቀጥል የአየር ኃይል አዛዥ አስታወቁ

M. Gen. Yilma Merdassa

የጁንታው እስትንፋስ ከጥቅም ውጭ መኾኑ ተገለጸ

ኢዛ (ረቡዕ ኅዳር ፪ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. November 11, 2020)፦ የኢትዮጵያ አየር ኃይል ጠላት ሊጠቀምባቸው ያሰባቸውን ምርጥ ዒላማዎች በመደብደብ ከጥቅም ውጭ ማድረጉንና “ጁንታው ለሕግ እስኪቀርብ ድረስ ጥቃታችንን እንቀጥላለን” ሲሉ የአየር ኃይል ዋና አዛዥ አስታወቁ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የሰሜን ዕዝን መገናኛ በመቁረጥ ሠራዊቱን በማስጨፍጨፍ የተጠረጠረው ጄኔራል ተያዘ

ሜጀር ጄኔራል ገብረመድኅን ፍቃዱ (ወዲ ነጮ)

ከጄኔራሉ በተጨማሪ 16 ተባባሪ ግብረአበሮቹም ተይዘዋል

ኢዛ (ማክሰኞ ኅዳር ፩ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. November 10, 2020)፦ በሰሜን ኢትዮጵያ መቀሌ የሚገኘውን የሰሜን ዕዝ ከማዕከል ጋር እንዳይገናኝና የመገናኛ ሥርዓቱ እንዲቋረጥ በማድረግ፤ በጁንታው የሕወሓት ቡድን በሰሜን ዕዝ ሠራዊት ላይ ጥቃት እንዲፈጽም ሲያመቻቹ የነበሩ ጄኔራል መኮንኖች በቁጥጥር ሥር ዋሉ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

“ጁንታው የሕወሓት ቡድን ሬሳችንንም ጭምር ነው ጅብ ያስበላው” ሌ/ጄ ባጫ ደበሌ

L. Gen. Bacha Debele

ድርጊቱን የፈጸሙትና የጁንታው ተባባሪዎች የሠራዊቱ አባላት፣ የትግራይ ክልል ልዩ ኃይል፣ ሚሊሻዎች እና የኦነግ ሸኔ ናቸው

ኢዛ (ማክሰኞ ኅዳር ፩ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. November 10, 2020)፦ በመቀሌ የመሸገው የሕወሓት ጁንታ ቡድን በሰሜን ዕዝ ሠራዊት ላይ የፈጸመው አረመኔያዊ ድርጊት፤ የተሰዉ የአገር መከላከያ ሠራዊትን አስከሬን አውሬ እስከማስበላት የደረሰ ዘግናኝ ተግባር የተፈጸመበት ጭምር እንደነበር ሌ/ጄኔራል ባጫ ደበሌ አስታወቁ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ጠቅላይ ሚኒስትሩ የመቀሌውን ጁንታ ተገቢውን ቅጣት ሳያገኝ ለአፍታም አናርፍም አሉ

PM Abiy Ahmed

ድርድር ብሎ ነገር እንደማይታሰብ አረጋገጡ

ኢዛ (ማክሰኞ ኅዳር ፩ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. November 10, 2020)፦ ስግብግቡንና አረመኔውን የመቀሌ ጁንታ ለፍትሕ ቀርቦ ተገቢውን ቅጣት ሳያገኝ ለአፍታም ቢኾን አናርፍም ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ገለጹ። ከጁንታው ጋር ምንም ዐይነት ድርድር እንደማይታሰብ አሳውቀዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ