በጎንደርና በባሕር ዳር የተተኮሱት ሮኬቶች ናቸው

Gonder

የጁንታው ቡድን ሮኬቱን እንደተኮሰ በአቶ ጌታቸው ረዳ በኩል አስታውቋል

ኢዛ (ቅዳሜ ኅዳር ፭ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. November 14, 2020)፦ ትናንት ምሽቱ አምስት ሰዓት አካባቢ በጎንደር እና በባሕር ዳር ከተሞች ላይ የተተኮሰው ሮኬት መኾኑ ሲረጋገጥ፤ ይህንንም የጁንታው ቡድን ስለመፈጸሙ ተረጋግጧል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ዶ/ር ሙሉ ነጋ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኾነው ተሰየሙ

Dr. Mulu Nega

በጊዜያዊ አስተዳደሩ በክልሉ የሚንቀሳቀሱ ፓርቲዎች ይካተታሉ

ኢዛ (ዓርብ ኅዳር ፬ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. November 13, 2020)፦ በትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኾነው እንዲያገለግሉ ዶ/ር ሙሉ ነጋ መሰየማቸው ተገለጸ። ሹመቱን የሰጡት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ናቸው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የአፍሪካ ሕብረት የጸጥታ ኃላፊን አነሳ

Chairperson of the African Union Commission Moussa Faki

ሜ/ጄኔራል ገብረእግዚአብሔር መብራቱ ከኃላፊነታቸው ተነስተው ብርጋዲየር ጄኔራል ኃይሉ ጎንፋ ተተኩ

ኢዛ (ዓርብ ኅዳር ፬ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. November 13, 2020)፦ የመከላከያ ሚኒስቴር የአፍሪካ ሕብረት የጸጥታ ኃላፊ በመኾን ሲያገለግሉ የቆዩት ሜጀር ጄኔራል ገብረእግዚአቤር መብራቱ መለስ ከኃላፊነታቸው እንዲነሱና በምትካቸው አዲስ ኃላፊ መሾሙን ባስታወቀው መሠረት፤ ሕብረቱ ኃላፊውን አሰናበተ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በሕወሓት ባለቤትነት በሚመራው ሱር ኮንስትራክሽን 23 የረዥም ርቀት መገናኛ ራዲዮኖች፣ 92 የእጅ መገናኛዎች፣ 67 የስልክ መጥለፊያ መሣሪያዎች ተያዙ

የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጌቱ አርጋው (ግራ) እና በሦስት ቀናት ውስጥ በአዲስ አበባ ከተያዙት ሕገወጥ መሣሪያዎች በጥቂቱ

242 የሕወሓት ተላላኪዎች ተይዘው ምርመራ እየተጣራባቸው ነው
በሦስት ቀናት 744 የጦር መሣሪያዎችና 4628 ጥይቶች ተይዘዋል

ኢዛ (ሐሙስ ኅዳር ፫ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. November 12, 2020)፦ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን በከተማዋ በሦስት ቀናት በተደረገ ፍተሻና ብርበራ 744 የጦር መሣሪያዎች፣ 4628 ጥይቶች፣ እንዲሁም የሕወሓት ጁንታ ቡድንን ተልዕኮ ተቀብለው ለማስፈጸም ሲንቀሳቀሱ የተገኙ 242 ተላላኪዎችን መያዙን አስታወቀ። ሕወሓት (ኤፈርት) በሚያስተዳድረው ሱር ኮንስትራክሽን ድርጅት ውስጥ ደግሞ ለሕገወጥ ተልዕኮ ማስፈጸሚያ ሊውል የነበረ 115 ልዩ ልዩ የመገናኛ ራዲዮኖች (23ቱ ለረጅም እርቀት ወይም በትከሻ የሚታዘሉ)፤ የጦር መሣሪያዎች፣ 67 የስልክ ግንኙነቶችን ለመጥለፍ የሚያችል መሣሪያ፣ ከአንድ ግለሰብ ላይ 350 ሲም ካርዶች፣ በተለያዩ ተቋማት ስም የተቀረጹ 6 ማሕተሞች፣ አንድ ግለሰብ በተለያየ ስም ያወጣው 7 ፓስፖርቶች መያዛቸውን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጌቱ አርጋው ገልጸዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ወንጀል የፈጸሙ 96 የጁንታው አባላትን አድኖ ለመያዝ የፍርድ ቤት ትእዛዝ ወጣ

የጁንታው ሕወሓት ቡድን አባላት

32ቱ ከፍተኛ የጦር መኮንኖች ናቸው

ኢዛ (ሐሙስ ኅዳር ፫ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. November 12, 2020)፦ የፌዴራል ፖሊስ የአገር ክህደት ወንጀል በፈጸሙ 96 የጁንታው ሕወሓት ቡድን አባላት ላይ የፍርድ ቤት ማዘዣ እንዳወጣባቸው አስታወቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

14 የግል ጥበቃ ኤጀንሲዎች ታገዱ

የኢፌ.ዲ.ሪ ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን

አብዛኞቹ በቀድሞ የሕወሓት መኮንኖች የተቋቋሙ ነበሩ

ኢዛ (ሐሙስ ኅዳር ፫ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. November 12, 2020)፦ የጁንታው የሕወሓት ቡድን ተልዕኮ በማስፈጸም ተደርሶባቸዋል የተባሉና ከተቋቋሙበት ዓላማ ውጭ ሲሠሩ የተደረሰባቸውን 14 የግል የጥበቃ ኤጀንሲዎችን ማገዱን የፌዴራል ፖሊስ አስታወቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የሰሜን ዕዝ የራዲዮ መገናኛ በመጥለፍ የተጠረጠሩ ከፍተኛ መኮንኖች ፍርድ ቤት ቀረቡ

ሜጀር ጄኔራል ገብረመድኅን ፍቃዱ (ወዲ ነጮ)

በአገር ክህደት ጭምር ይጠየቃሉ

ኢዛ (ሐሙስ ኅዳር ፫ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. November 12, 2020)፦ የሰሜን ዕዝን የራዲዮ መገናኛ በመጥለፍ የተጠረጠሩት የመከላከያ ኮምዩኒኬሽን ኃላፊ ሜጀር ጄኔራል ገብረመድኅን ፍቃዱን ጨምሮ ሰባት ጄኔራሎች አገርን በመክዳት ወንጀልና ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን ለመናድ በማሰብ ወንጀል ፍርድ ቤት ቀረቡ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በተለያዩ የአገሪቱ ክልሎች ጁንታውን የሚቃወሙ ሰልፎች ተካሔዱ

በተለያዩ የአገሪቱ ክልሎች ጁንታውን በመቃወም ዛሬ ሐሙስ ኅዳር 3 ቀን 2013 ዓ.ም. የተካሔዱ ሰልፎች

መንግሥት ሕግ የማስከበሩን ሥራ አጠንክሮ እንዲቀጥል ማሳሰቢያ ተሰጠ

ኢዛ (ሐሙስ ኅዳር ፫ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. November 12, 2020)፦ የሕወሓት ጽንፈኛ ቡድን በቅርቡ በሰሜን ዕዝ የመከላከያ ሠራዊት ላይ ያደረሰውን ጥቃት የሚቃወሙ ሰልፎች ዛሬ ሐሙስ ኅዳር 3 ቀን 2013 ዓ.ም. በተለያዩ የክልል ከተሞች ተካሒደዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ዶክተር ደብረጽዮንን ጨምሮ 38 የሕወሓት አባላት ያለመከሰስ መብት ተነሳ

አቶ ጌታቸው ረዳ እና ዶክተር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል

ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ በተለያዩ ወንጀሎች ይፈልጋቸዋል

ኢዛ (ሐሙስ ኅዳር ፫ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. November 12, 2020)፦ የቀድሞ የትግራይ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ደብረጽዮን ገብረሚካኤልን ጨምሮ 38 የሚኾኑ የሕወሓት አባላትና ሌሎች ግለሰቦች ያለመከሰስ መብታቸው እንዲነሳ ተወስኗል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ