ምርቃትና እርግማን (ከትንሣዔ)
ምርቃትና እርግማን
ከትንሣዔ - ሐምሌ 2000 ዓ.ም. (በፒ.ዲ.ኤፍ. አስነብበኝ)
የእውኑን አለም በምኞት ዳበሳ፣
ስንዘግን ስንበትን ስንወድቅ ስንነሳ።
ወይም ስንማማል እቴ ሙች እቴ ሙች፣
ዘመን እያለፈ ዘመን ይልና ከች፤
በታሪክ አጊጠን የዛሬን ተዋርደን፣
እንዲህ ነው እንዲያ ነው ጥግ ይዘን ዳር ቆመን።
አልያም ስንሰደድ ከሀገር ስንጠፋ፣
አገርም ሲሸቀጥ ጎርቤት ሲስፋፋ።
አንዴ በምርቃት አንዴ በእርግማኑ፣
ስንቀባባበት መሽቶብናል ቀኑ።
ነገንም ብንተወው ሰጥተነው ለእግዜሩ፣
መክሊቱን ለጣለ የርሱም ዝግ ነው በሩ።
ሙሉውን አስነብበኝ ...


