ምርቃትና እርግማን (ከትንሣዔ)

ምርቃትና እርግማን

ከትንሣዔ - ሐምሌ 2000 ዓ.ም. (በፒ.ዲ.ኤፍ. አስነብበኝ)  

 

የእውኑን አለም በምኞት ዳበሳ፣

ስንዘግን ስንበትን ስንወድቅ ስንነሳ።

ወይም ስንማማል እቴ ሙች እቴ ሙች፣

ዘመን እያለፈ ዘመን ይልና ከች፤

በታሪክ አጊጠን የዛሬን ተዋርደን፣

እንዲህ ነው እንዲያ ነው ጥግ ይዘን ዳር ቆመን።

አልያም ስንሰደድ ከሀገር ስንጠፋ፣

አገርም ሲሸቀጥ ጎርቤት ሲስፋፋ።

አንዴ በምርቃት አንዴ በእርግማኑ፣

ስንቀባባበት መሽቶብናል ቀኑ።

ነገንም ብንተወው ሰጥተነው ለእግዜሩ፣

መክሊቱን ለጣለ የርሱም ዝግ ነው በሩ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የተሰደዱ ጠጉሮች (ከትንሣዔ)

የተሰደዱ ጠጉሮች

ከትንሣዔ (ሰኔ 2000 ዓ.ም.) (በፒ.ዲ.ኤፍ. አስነብበኝ)

 

የጊዜ ዑደቱ በራስ ላይ የመጣ፣

ወለላዬም ሽበት ትንሣዔም መላጣ።

ሆነን አየንና በዘመን መስተዋት፣

ቁልቁልም ወረድን ወጣንም አቀበት፤

ግራ አጋባንና መመለጥ መሸበት።

ተረት ሆነን ልንሞት ታሪክ ሳንሰራ፣

ብልጭ ብለን ጥፍት እንደ ባለ ተራ።

እያልኩ ሳስተውል ሳስብ ስመረምር፣

እጅግ ጥልቅ ሆነብኝ የተፈጥሮ ምስጢር።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ጀግና አይደለንም ወይ? (ከወለላዬ)

ጀግና አይደለንም ወይ?

ከወለላዬ (This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it.)

(Read on PDF)

መቼም የሚያቃጥል የሚያጨስ አይጠፋ

አንዱ ትናንትና እሰው ፊት በይፋ

በጀግንነታችን እንደሚጠራጠር

ቃላት አሳምሮ ሰማሁኝ ሲናገር

ሙሉውን አስነብበኝ ...