ይህን ነበር የምፈራው

የአንባብያን ድምፅ: 4 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Inactive

ብሥራት ደረሰ - ከአዲስ አበባ

ማስታወቂያ!
የመጀመሪያው የአማራ ዓለም አቀፍ ጉባኤ

ወያኔን እግዜር ይይለት! የኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች እንደሆኑ የሚታመኑ ምዕራባውያንም ይሁኑ ምሥራቃውያን እነሱም እግዜር ይይላቸው! በተለይ በተለይ የነዚህ የውጭ ምንደኛ ጠላቶቻችን አሽከር በመሆን ላለፉት 42 ዓመታት ኢትዮጵያን እንደደሮ ሲበልቱና ሕዝቧን እንደአሻሮ ሲቆሉ ሀብት ንብረቷንም በግላጭ ሲዘርፉና ወደጎሬኣቸው ሲያጓጉዙ የነበሩ ሰሜነኛ ናዚዎችና ፋሽስቶች ዘር አይውጣላቸው። የጀመሩት እንደጪስ በንነውና እንደጤዛ እረግፈው ወደታሪክ ትቢያነት የመለወጥ ትንቢታዊ የመጨረሻ ዕጣ በቅርብ ጊዜ ተጠናቆ ሀገራችን ነፃ እንድትወጣ ፈጣሪ ይርዳን። አሜን።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ፖለቲካም እንደ ሳይንስና እንደ ሂሳብ መታየት ያለበት ወይስ ሳይንስ-አልባ!

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

ፈቃዱ በቀለ (ዶ/ር)

መግቢያ

ፖለቲካን በሚመለከት ከሂሳብ አንፃር ሳይሆን ከሳይንስ አንፃር ብቻ ለመጻፍ ሳወርድ ሳወጣ፣ አቶ ካሳሁን ነገዎ የኤስ ቢኤስ ጋዜጠኛና ቃለ-መጠይቅ ጠያቂ እ.አ በ03.04.2017 ዓ.ም በፖለቲካና በሂሳብ መሀከል ስላለው ግንኙነት የሂሳብ አስተማሪና ተመራማሪ ለሆኑት ፕሮፌሰር ደጀኔ አለማየሁ ያቀረበላቸውን ጥያቄዎችና መልሶቹን ካዳመጥኩኝ በኋላ በዚህ አርዕስት ላይ ለመጻፍ ተገፋፋሁ። በመሰረቱ ለቀረቡት ጥያቄዎች የተሰጡትን መልሶች ካዳመጥኩኝ በኋላ በመልሱ በጣም መርካቴ ብቻ ሳይሆን፣ አገራችን ኢትዮጵያ እንደዚህ ዐይነት ምሁራንን ለማፍራት ችላለች ወይ? ብዬ ራሴን ትንሽ ለማጽናናት ሞከርኩኝ። በመሰረቱ ፕሮፌሰር ደጀኔ ፖለቲካ እንዴት ከሂሳብ ጋር ሊያያዝ ይችላል ተብለው ለተጠየቁት ጥያቄና ስለፖለቲካ ምንነት በደንብ ስላብራሩና አጥጋቢ መልስም ስለሰጡ ይህ ጽሁፌ የሳቸውን አተናተን የሚደግፍ ነው። ትንሽ የማክልበት ነገር ቢኖር ፖለቲካ የሚባለው ሕብረተሰብዓዊ ፕሮጀክት በአውሮፓ ምድር ውስጥ እንዴት አድርጎ ቀስ በቀስ ሊዳብር እንደቻለና ለዕድገትና ተቻችሎ ለመኖር የሚያስችል መሳሪያ በመሆን የተለያየ አመለካከት ባለቸው ፓርቲዎችና የሕብረተሰብ ክፍሎች ዘንድ ተቀባይነትን እንዳገኘ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ጠቅላይ ሚንስትራችንን በዚህች ትንሽ አጋጣሚ እንወቅ

የአንባብያን ድምፅ: 4 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Inactive

ነፃነት ዘለቀ

PM Haliemariam Desalegn
ጠ/ሚ ኃይለማርያም ደሳለኝ

እንደአካሄድ ጠቅላይ ሚንስትሩን የማያውቅ ወይም ለማወቅ የማይጓጓ ዜጋ መኖር የለበትም። ምክንያቱም ጠቅላይ ሚንስትር ማለት ከእያንዳንዱ ዜጋ ልብ ውስጥ መጥፋት የሌለበት የሁሉም አለኝታና ከአባትና እናት የማይተናነስ ቦታ ያለው ነውና። አንድ ዕድለኛ ቤተሰብ ውስጥ እናትና አባት ይኖራሉ። አንዱ ቢጎድል ከሁለት አንዱ ይኖሩና ክፍተቱን በተቻለ መጠን ለመሙላት ይሞክራሉ። ሁለቱም ከጎደሉ ግን በተለይ ልጆች ትንንሽ ከሆኑ ብዙ ችግር ይፈጠራል። በተጨማሪም የወላጆች መኖር ብቻውን ምንም ማለት የማይሆንበት አጋጣሚ መኖሩንም መዘንጋት አይገባም።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

“አሥር ቢሊዮን” ብሩ በእርግጥ የወጣቱን የሥራ አጥነት ያቃልላል?

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

ዮፍታሔ

“ሪፖርተር” ከሰሞኑ ካወጣቸው ዘገባዎች አንዱ "ከወጣቶች አሥር ቢሊዮን ብር በጀት ተጠቃሚ ለመሆን ከሦስት ሚሊዮን በላይ ሥራ አጦች ተመዘገቡ" ይላል። ሲጀመር ሕወሓት ይህንን እቅድ ድንገተኛ ደራሽ በሆነ መንገድ በፓርላማ እንዲጸድቅ ያደረገችው የተፈጠረው ሕዝባዊ አመጽ አንዱ መነሻ ምክንያት የወጣቶች ሥራ አጥነት ስለሆነ ሥራ አጥነቱን በመቀነስ ሕዝባዊ አመጹን ማብረድ እችላለሁ ከሚል ስሌት ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የሕይወት ዋጋ

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

ፕ/ር መስፍን ወልደማርያም

በተደረመሰው ቆሻሻ ሕይወታቸውን ያጡ ወገኖቻችን የቀብር ሥነሥርዓት
በተደረመሰው ቆሻሻ ሕይወታቸውን ያጡ ወገኖቻችን የቀብር ሥነሥርዓት፣ ገብረክርስቶስ ቤተክርስቲያን፣ አዲስ አበባ፣ መጋቢት ፬ ቀን ፳፻፱። (ፎቶ፡ AP)

በ2009 ዓ.ም. ቆሼ የሚባል ሠፈር ወይም መንደር ተፈጠረ፤ ቆሼ ማለት ቆሻሻን ማቆላመጫ ነው፤ ቆሻሽዬ ማለት ነው፤ ቆሼ የቆሻሻ ተራራ ነው፤ በዚያ የቆሻሻ ተራራ ዙሪያ መሄጃ የሌላቸው ሰፈሩበት፤ ጥንት ሴትዮዋ እንዳለችው፡-

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ሦስቱ መስቀለኛ መንገዶች! ... ታሪክ እራሱን እንዳይደግም

የአንባብያን ድምፅ: 4 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Inactive

መስቀሉ አየለ

ደርግ የሚባል ለኮንጎ ዘማቾች ደመወዝ ለማስጨመር ከየክፍለጦሩ የተወከለ የወታደሩ ኮሚቴ ግዜያዊ ጣቢያውን አዲስ አበባ በሚገኘው አራተኛው ክፍለ ጦር አቋቁሞ፤ ከኃይለሥላሴ መንግሥት ጋር መደራደር ጀመረ። ነገሩ በወቅቱ ከነበሩት ካቢኔቶች በላይ ሄደና እንደ ቀልድ ከንጉሡ በመድረሱ አጋጣማውን እየተጠቀመ ወደ ቤተመንግሥቱ ወጣ ገባ ለማለት ዕድል ያገኘው ይኽ ኮሜቲ የንጉሡን ክፉኛ መድከም ለማስተዋል ግዜ አልወሰደበትም።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ