"... ሕገወጦችን ከምርጫ በኋላ እንከሳለን ..." አቶ መለስ ዜናዊ

Star InactiveStar InactiveStar InactiveStar InactiveStar Inactive

ተሻገር በላይ This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it.

"... ሕገወጦችን ከምርጫ በኋላ እንከሳለን ..." የሚለው ንግግር የህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ ሊቀመንበር፣ የኢህአዲግ ሊቀመንበር፣ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስቴር እና የጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥ የሆኑት አቶ መለስ ዜናዊ ሰሞኑን ከተናገሩት ውስጥ የተወሰደ ነው። ይህ አባባላቸው አዲስ ሆኖብኝ ሳይሆን ከምርጫ ሂደት ጋር ሲታይ አግባብ የሌለው መሆኑን ወዳጆቻቸውና ደጋፊዎቻቸው ማየት ቢችሉ ብዬ ነው። ሙሉውን አስነብበኝ ...

የአንድነቱ ቀኝ አዝማች

Star InactiveStar InactiveStar InactiveStar InactiveStar Inactive

ዕድሜዓለም

ከዓመት በፊት በኢትዮጵያ ዛሬ ድረ-ገጽ ላይ “አንድነትም እንደ መአህድ ብርቱካንም እንደ አስራት” በሚል ርዕስ ጽሁፍ ወጥቶ ነበር። ፀሐፊው መአህድ ተመስርቶ በብቃት መንቀሳቀስ እንደጀመረ ከውስጥም ከውጪም የገጠመውን ፈተና አመላክተው፤ መሪውን ፕ/ር አስራትን ወደ እስር ቤት በመላክ ፓርቲውን እንዴት መቆጣጠር እንደተቻለ የራሳቸውን እይታ የጋዜጠኛው ማስታወሻ ደራሲ ተስፋዬ ገብረአብ በሰጠው ምስክርነት አስደግፈው አሳይተውናል። በንጽጽርም ከ10 ዓመት በኋላ አንድነትና መሪው ብርቱካን ተመሳሳይ ዕጣ እንደገጠማቸው ፀሐፊው በጊዜ በቦታና በድርጊት እያመሳከሩ ነግረውናል።  ሙሉውን አስነብበኝ ...

ይድረስ ለአቶ ገብሩ አስራት፣ ከመርስኤ ኪዳን

Star InactiveStar InactiveStar InactiveStar InactiveStar Inactive

መርስኤ ኪዲን

እንዳሁኑ ሳይሆን ቀድሞ “ገብረማሪያም” ምርጥ ከሚባሉ ስሞች አንዱ ነበር። እናም አንዳንድ ዓይነደረቅ ሰዎችን ለመግለፅ በትግርኛ ”ዘይሓፍር ድሙ ገብረማሪያም ሽሙ” የሚል አባባል አለ። ትርጉሙም “የማያፍር ድመት ስሙ ገብረማሪያም ነው” ማለት ነው። ይህን አባባል ለመጠቀም ያስገደደኝ በምርጫ ተፎካካሪ ፓርቲዎች መካከል ባለፈው ሣምንት በተደረገው ክርክር መድረክን ወክለው የተገኙት ሰው አቶ ገብሩ አስራት መሆናቸውን ሳይ የተፈጠረብኝ ግርምት ነው። የክርክሩ አጀንዳ “ሰብዓዊ መብት፣ የሕግ የበላይነትና መልካም አስተዳደር” ስለነበር ነው ግራ መጋባቴ። ምክንያቱም አቶ ገብሩ የትግራይ ፕሬዝዳንት እያሉ ትግራይ ውስጥ የዩንቨርስቲ ተማሪ ስለነበርኩ፤ የእሳቸው አስተዳደር ምን ይመስል እንደነበር ጠንቅቄ ስለማውቅ ነው። ሙሉውን አስነብበኝ ...

የሰብዓዊ መብት ጥሰትና የዘር ማጥፋት ወንጀል በኢትዮጵያ (ንጉሤ ጋማ)

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

በኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት ጥሰትና የዘር ማጥፋት ወንጀል አስመልክቶ በለንደን የተካሄደ ስብሰባታላቅ ህዝባዊ ስብሰባ በእንግሊዝ ፓርላማ ተካሄደ

ንጉሤ ጋማ

የሁሉም ፓርቲዎች የፓርላማ ቡድን በ3ኛው ዓለም ትብብር (All Party Parliamentary Group on the Third World Solidarity) በመባል የሚጠራው ድርጅት በታላቋ ብሪታኒያ ከሚገኙ የኢትዮጵያ ማኅበረሰብ አባላት ጋር በመተባበር ያዘጋጀው እን በኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ላይ የተወያየ ታላቅ ህዝባዊ ስብሰባ በለንደን ተካሄደ። ሙሉውን አስነብበኝ ...

ቢያንስ ዶሮዋን አንሆንም?

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

Dorowaኩችዬ - መጋቢት 1 ቀን 2002 ዓ.ም. (ማርች 10 ቀን 2010 እ.ኤ.አ.)

ሹም መሆን ብዙ ፈተና አለው ወዳጄ! አንዲት አነስተኛ ወረዳ ውስጥ አስተዳዳሪ ሆኖ የተመረጠ ሰው የህዝቡን ተሳትፎ ለማግኘት ቁርጥ ሃሳብ ያደርጋል። የነጋዴው፤ ያስተማሪው፤ የተማሪው፤ የገበሬው በር አልቀረውም። የሁሉንም አንኳኳ። አንዱን ቀን እግሩ ካንድ ገበሬ ቤት ይጥለውና ... 

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ለኢ/ር ግዛቸው ሽፈራው

Star InactiveStar InactiveStar InactiveStar InactiveStar Inactive

ወዶ የዋጡትቅልጥም ከፍርምባ ይጥም

ታምራት ታረቀኝ

ከኢ/ር ግዛቸው ጋር ለመጨረሻ ግዜ ተገናኝተን የተነጋገርነው ሰኔ 11 ቀን 2001 ዓ.ም. በእኔ ጠያቂነት በርሳቸው ቢሮ ውስጥ ነው። ከቀትር በኋላ። ርሳቸው ጋር ለመነጋገር ምክንያቶቼ ሁለት ነበሩ። አንደኛው ሰኔ 8 እና 9 በነበረው የብሔራዊ ምክር ቤት ስብሰባ ላይ በሌሎች ሰዎች እየተመሩ ስህተት ሲፈጽሙ ማየቴ ሲሆን፤ ሁለተኛው ደግሞ ዋና ፀሐፊ አስራት ጣሴ ከኃላፊነት በመሸሽ በምክትላቸው ወጪ የሚያደርጉዋቸው ደብዳቤዎች ጉዳይ ነበር። ሙሉውን አስነብበኝ ...