“የብሔርና የግለሰብ መብት ጥያቄ በኢትዮጵያ - ትናንትናና ዛሬ” በዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ
ባለፈው ሣምንት ቅዳሜ ታህሳስ 18 ቀን 2001 ዓ.ም. “መድረክ ለዲሞክራሲያዊ ምክክር በኢትዮጵያ” (የምክክር መድረክ) የተሰኘው ድርጅት በኢምፔሪያል ሆቴል ባዘጋጀው የውይይት መድረክ ላይ ስድስት ምሁራን የውይይት ጽሑፍ ማቅረባቸውን መዘገባችን አይዘነጋም። የቀድሞው የኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት የነበሩት ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳም አንዱ ጽሑፍ አቅራቢ የነበሩ ሲሆን፣ “የብሔርና የግለሰብ መብት ጥያቄ በኢትዮጵያ - ትናንትናና ዛሬ” በሚል ርዕስ የመወያያ ጽሑፋቸውን አቅርበዋል።
ሙሉውን አስነብበኝ ...
“ሕገ አራዊት” የተፈጥሮ ሕግ ነው፤ በደመ-ነፍስ የሚንቀሳቀሱ ኹሉ ለመራባት የሚያስችላቸውን ግዴታቸውን የሚፈጽሙት በሕገ አራዊት ነው። የቀደመው አሁን ከአለው አይለይም፤ የወደፊቱ ከአሁኑ እንደማይሻል የታወቀ ነው። የቀድሞውም በጉልበት ነው፤ የአሁኑም በጉልበት ነው፤ የወደፊቱም በጉልበት ነው። የሕገ አራዊት መሠረቱ ጉልበት ብቻ ነው። ምግብ የሚገኘው በጉልበት ነው፤ ጉልበት ያለው ይበላል፤ ጉልበት የሌለው ለጉልበተኛው ምግብ ይሆናል፤ ጉልበት ያለው ይንደላቀቃል፤ ጉልበት የሌለው በየጉድጓዱ ይሽሎከለካል።



