ኢህአዴግ ዳመነበት እንጅ አልመሸበትም

የአንባብያን ድምፅ: 4 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Inactive

ፍትሕ ይንገሥ (የኢትዮጵያና የህዝቦቿ ሁኔታ ከሚያሳስባቸው ዜጎች አንዱ)

ከሁሉ በፊት አንባቢያን ሊገነዘቡት የሚገባው ጉዳይ ይህ ፅሁፍ ጥናት ላይ የተመሰረተ አለመሆኑን ነው። መነሻው በዋነኛነት የግል ትዝብት ሲሆን ከሌሎች የኢህአዴግ ደጋፊዎችና ገለልተኛ ሊባሉ ከሚችሉ ወገኖች ጋር የተደረጉ ውይይቶችም ውጤት ጭምር ነው። ለማንኛውም ግን ፅሁፉ ላይ የተነሱትን ችግሮች በተመለከተ ኢህአዴግ እንደተለመደው የተከላካይ (defensive) መንፈስ ይዞ ባያያቸው ይመረጣል። ይልቁንም የተነሱት ችግሮች አሉ ወይስ የሉም ብሎ በቅንነት ቢያያቸውና ራሱን ቢፈትሽ ያጠናክሩታል እንጅ ለጉዳት አይዳርጉትም። ይህን ለማድረግ ደግሞ የግድ የሮኬት ሳይንስ ማጥናት አያስፈልግም።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በ40 ሚሊየን ብር ያለአግባብ ግዥ ሊጠየቁ የሚገባቸው ፕሮፌሰር ይፍሩ ብርሃነን ለሚኒትርነት ማዕረግ?

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

Prof. Yifru Berhaneከጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ሠራተኞች አንዷ

ጥቅምት 22 ቀን 2009 ዓ.ም.፡- ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ወደ ሥልጣን ከመጡ በኋላ በድጋሚ ያቋቋሙትን ካቢኔ ከአንድ ዓመት ጊዜ ቆይታ በኋላ በማፍረስ እንደ አዲስ ያደራጁትን አዲስ ካቢኔ ጥቅምት 22 ቀን 2009 ዓ.ም. ለሕዝብ አሳውቀዋል፤ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ካዋቀሩት ካቢኔ ውስጥ አብዛኞቹ ከከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የመጡ መሆናቸው እስከ አሁን ካለው አወቃቀር ልዩ ያደርገዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

እውነተኛ "አማራጭ ኃይል"

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

Young and old generationዮፍታሔ

ከሚነገረውና ከሚጻፈው በላይ የማይነገረውና የማይጻፈው እየበለጠ ነው።

በተቃዋሚዎች መካከል በውጭም ሆነ በአገር ቤት፣ በኢትዮጵያም ሆነ በኤርትራ የሚካሄደው ሽኩቻና መገፋፋት በአረጋውያኑ እና በወጣቱ መካከል የሚካሄድ እየመሰለ ነው።

አረጋውያኑ ዘንድ ስም፣ ልምድና የውጭ ግንኙነት አለ። ወጣቶቹ ዘንድ አፍላ ኃይል፣ ቴክኖሎጂና የውስጥ ግንኙነት አለ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

መልዕክት፤ ለኢትዮጵያ አገራዊ ንቅናቄ መስራቾች

የአንባብያን ድምፅ: 4 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Inactive

Ethiopian National Movement meetingይገረም አለሙ

የተቀዋሚዎች ብዛት የርስ በርስ ሽኩቻና የጎንዮሽ ትግል ለወያኔ ዕድሜ መርዘም ዋናው ምክንያት መሆኑ አሌ የማይባል ነው። የድርጅቶቹ ዓላማ ሳይሆን የመሪዎቹ ፍላጎት አይታረቄነት ተባብሮ ለመሥራት የማያስችል ሆኖ ውሾቹም ይጮኻሉ፣ ግመሉም ይሄዳል እየተባለ ሃያ አምስት ዓመት ዘልቀናል።

በተግባር እንዳየነው ለፓርቲዎቹ መብዛትም ሆነ ለመተባበር አለመቻል ዋናው ችግር የአደረጃጀትና የትግል ስልት ወይም የዓላማና ግብ ልዩነት ሳይሆን፤ የትግል ጽናትና ቁርጠኝነት አለመኖርና ከሚነገረው በስተጀርባ የተደበቀ የመሪዎች ፍላጎት መኖር ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የ"ጥልቅ ተሃድሶ" ድራማ ተጀምሯል!

የአንባብያን ድምፅ: 4 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Inactive

Ethiopian parliamentክንፉ አሰፋ

በቤተ ሙስና፣ የ"ጥልቅ ተሃድሶ"ው ድራማ ተጀምሯል! የእርስ በርስ እና ራስን በራስ መተካካት ቧልት እና ፌዝ።

ከመጋረጃው ጀርባ ስብሃት ነጋ፣ አቦይ ጸሃይ፣ ጌታቸው አሰፋ፣ ደብረጽዮን እና በረከት ስምኦን የሚቆምሩትን ካርታ፤ ኃይለማርያም ደሳለኝ እንደቬጋስ አጫዋች ፊት እያመጣ ይዘረጋዋል። በዲዮጋን ያደረጉት አብዮታዊ እና ልማታዊ "ምሁራን" ፍለጋ ውጤት ነበረው። "የዶክተር ያለህ" ፍለጋ ጥቂት ታማኝ አገልጋዮችና፣ በርካታ ሮቦቶችን አስገኝቷል። "በዲሞክራሲ" በተመረጠው "የሕዝብ ምክር ቤት" የሚኒስትሮቹ ስም ይፋ በሆነ ግዜ፤ ለይስሙላ እንኳን ተቃውሞ፣ አልያም ድምጸ-ተአቅቦ ቢያደርግበት ድራማውን ያሳምረው ነበር። በሙሉ ድምጽ ጸደቀ ተባለ። የነዚህ ሮቦቶች ምርጫ የፍልፍሉን ቀልድ ያስታውሳል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

“የለውጥ ኃይሎች” ግልፅና ደፋር ውይይት ለመፍትሔና የጋራ ድል (ክፍል ሁለት)

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

Ermias Legesseኤርሚያስ ለገሰ

ጆቤ እንኳን ደህና አልመጣችሁ!!

ለህዝብ ውይይት መድረክ የተዘጋጀ (ሂውስተን/ቴክሳስ)

የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቭዥንና ራዲዮ(ኢሳት)

ጥቅምት/2016

ማስታወሻ

ይህ ጽሁፍ ከራሴ ውጭ የምሰራበትን የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቭዥንና ሬዲዮ (ኢሳት)ን ጨምሮ የማንንም አቋም አያንፀባርቅም።

መግቢያ

“የለውጥ ኃይሎች ግልፅና ደፋር ውይይት ለመፍትሔና የጋራ ድል” በሚል አቢይ ርዕስ ተከታታይ መጣጥፍ እየቀረበ ነው። ከዚህ ቀደም “በክፍል አንድ” በተሰራጨው ጽሁፍ ሁለት ቁምነገሮችን ለመዳሰስ ተሞክሯል። የመጀመሪያው፦ ግልጽና ደፋር ውይይት የምናደርግባቸው መሰረታዊ ምክንያቶች ምን እንደሆኑ ለመዘርዘር ተሞክሯል። ዛሬ አገራችን ያለችበት ሁኔታ የሚያሳስበው ዜጋ ባለመኖሩና አገር አደጋ ላይ በወደቀችበት ሁኔታ በመተማመን ላይ የተመሰረተና የጋራ ድል (win- win) በሚያረጋግጥ መልኩ ምክክር መካሄድ እንዳለበት የተገለጠበት ነው። መጣጥፍ በኢትዮጵያ ውስጥ የሥርዓት ለውጥ መምጣት አለበት በማለት የሚንቀሳቀሱት ሁሉም የለውጥ ኃይሎች የዛሬና የነገን ኢትዮጵያ እጣ ፋንታ በሚወስኑ መሰረታዊ ጉዳዮች ላይ ምን እንደሚያስቡ ለህዝቡ ማቅረብ እንዳለባቸው የሚጠይቅ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ