የተባበረችውን ኢትዮጵያን በጋራ እንገነባለን!

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

ገለታው ዘለቀ

We build ONE Ethiopia!

በቅርቡ በአንድ የኦሮሞ ወገኖች ስብሰባ ላይ አንድ ሰውየ፤ “ኦሮምያ ሰላም የምታገኘው ኢትዮጵያ ስትፈራርስ ነው፤ ኢትዮጵያ መፍረስ አለባት” አለ ተብሎ ሲራገብ እያየን ነው። እኔ በግሌ የዚህን ሰው ተልዕኮ ለመረዳት ቅንጣት ጊዜ አልወሰደብኝም። ከራሱ ከወያኔ በቀጥታ መልዕክት እየተቀበለ የሚሠራ የወያኔ ተቀጣሪ ነው፤ ወይም እያጃጃሉ በስልት የሚጠቀሙበት ሰው ነው። አለቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

“መፍራትና መጠንቀቅ ሰንደቅ ዓላማ ለብሰው ሀገር የሚያፈርሱትን ነው”

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

Ethiopian flagይገረም አለሙ

ከአሥራ አምስት ዓመት በፊት ነው ኢዴፓ በቅሎ ቤት በሚገኘው ጽ/ቤቱ ዕለተ ግንቦት 20ን አስመልክቶ አንድ ፕሮግራም አዘጋጅቶ ተገኝተናል። ከተናጋሪዎቹ አንዱ የነበሩት የወቅቱ የፓርቲው ሊቀመንበር ዶ/ር አድማሱ ገበየሁ ባደረጉት ንግገር ውስጥ፤ “መፍራትና መጠንቅ ካለብን ሰንደቅ ዓላማ ለብሰው እኛኑ መስለውና ተመሳስለው ሀገር የሚያፈርሱትን በመካከላችን የሚገኙትን ነው” የሚለው አረፍተ ነገር በአእምሮየ ተቀርጾ አብሮኝ ይኖራል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በጎሣ ትግል ወያኔ አይወድቅም፤ ቢወድቅም ውጤቱ አያምርም

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

መሳፍንት ዘፈረንሳይ ለጋሲዮን

Stop shouting

በኦሮሚያ ተቀጣጥሎ ወደተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች ለተዛመተው ሰላማዊ የፍትሕ ይገባኛል ጥያቄ፤ የግድያና የእስራት ምላሽ እየሰጠ ያለውና በቅርቡም ግለሰቦች፣ የፖለቲካ ድርጅቶች፣ የእምነት ተቋማት፣ የመገናኛ ብዙኀንና ዲፕሎማቶች ሳይቀሩ የመብት እንጥፍጣፊ እንዳይኖራቸው “በባርነት አዋጁ” የደነገገው የወያኔ ሥርዓት፤ ለሩብ ምዕተ ዓመት ሲሠራ የቆያውንና አሁንም እየሠራ ያለውን ሁሉ ያስተዋለ በሀገራችን የተከሰተውን ስር የሰደደ የፖለቲካ ቀውስ መረዳት አያዳግተውም።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኢሰመጉ ከየት ወዴት?

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

ፕ/ር መስፍን ወልደማርያም

አምስት ዓረፍተ ነገሮች

ኢሰመጉ መንፈሳዊ ተልዕኮ ያለው መንፈሳዊ ድርጅት ነው፤ ዓላማው በሰው ልጆች መሀከል የሚከተሉትን ተልዕኮዎች መዝራት ነው፡–

1.1. እኩልነትንና ነጻነትን
1.2. ፍቅርንና ስምምነትን
1.3. ፍትሕንና ሕጋዊነትን
1.4. ሰላምንና ማኅበረሰባዊ እድገትን
1.5. የእውነትንና የእውቀትን ብርሃን ማስፋፋትን

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ፀጉረ ልውጦች በፍራንክፈርት

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

በልጅግ ዓሊ

እህ ዛዲያማ
በአንድ ጎጆ
እህ!
አንድ ቁርንጮ ይነጠፍና
እህ!
አዋጅ በይፋ ይታወጅና
እህ!
ኃይል ያደራጃል ደግሞ እንደገና
እህ ዛዲያማ!
እህ ዛዲያማ! ምን ትለኛለህ?
ከየመንገዱ ሰብሰቦ ሲያስርህ
አይደለም እንዴ ገድሎ ሊጥልህ።
. . .
ወለላዬ

እነሆ ጀርመን ፍራንክፈርት ከተማ አለወትሮዋ በፀጉረ ልውጦች ከተሞላች ሰንበትበት አለች። ሀገራችን ያለው ህዝባዊ እምቢተኝነት እንቅስቃሴ ያስፈራቸው የወያኔ ጀሌዎችና ደጋፊዎች የተነሳውን እሳት ለመሸሽ በመዘየድ ወደ አውሮፓና ሰሜን አሜሪካ በተራቸው መፍለስ መጀመራቸው መሆኑ ነው። ይህ ትዕይንት የወያኔ ዘመን ሊያከትም መዳረሱን ጠቋሚ ክስተት ነው። ዛሬ በመካከላችን የምንሰማው ዱካ፣ በዓይናችን የምንቃኘው ወዛም ገጽታ፣ በየሱቁ የምናስተውለው ግርግር፣ የባለሥልጣን፣ የቱጃር ሚስቶችና ልጆች፣ እንዲሁም ዘመዶችና ቁባቶች መሆናቸውን አንዳች የሚያሳብቅ ነገር አለው። እንደው በጥቅል አነጋገር በከተማው ውስጥ በሰፊው የሚታዩት እነሱ ስለመሆናቸው ብዙ ዋቢ ማቅረብ የሚያስፈልግ ከቶ አይመስለኝም።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በተለይ ለኦሮሞ ልሂቃን የተላከ ማስታወሻ

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

Oromo protestነፃነት ዘለቀ

መድኃኒት ከምን እንደሚሠራ አለማወቃችን በጄ እንጂ፤ ብዙ ፈዋሽ መድኃኒቶች የሚቀመሙት ከመርዝና ብዙም ከማንወዳቸው ነገሮች ነው። ግን መዳን ስላለብን ሐኪምና ዐዋቂ እንድንወስዳቸው የሚመክሩንን የሚቀቡም ሆኑ የሚዋጡ መድኃኒቶች አለማመንታት እንወስዳቸዋለን። በቤታችንስ ስንቶቻችን ነን የገዛ ሽንታችንን የምንጠጣ? አዎ! መድኃኒት ነው ከተባለ የጅብ ጉበትም ይበላል፤ የአህያ ወተትም ይጠጣል። ዋናው ከሚያሰቃየን ደዌ መፈወሱ ነው። “ምንም ቢያስቀዝን ጮማ” ብሎ ነገር በጭንቅ ወቅት አይሠራም። አሁን ያለንበት ሀገራዊ ድባብም እንዲሁ በጣም አስጨናቂና አሳሳቢ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ