በኢትዮጵያ ያለው ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓት ነውን? (ክፍል አንድ)

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

ይገረም አለሙ

ሕገ መንግሥታዊውን ሥርዓት በኃይል ለማፈረስ የሚል ክስ በሀገራችን ተራና የተለመደ ነገር ከሆነ አመታት ተቆጥረዋል። በስፋት የታወቀው፣ ምን አልባትም የተጀመረው በቅንጅቶች ክስ ይመስለኛል። ለሥልጣን ያሰጋሉ ተብሎ የተገመቱ ዜጎችን በዚህ እየወነጀሉ በመገናኛ ብዙሀን መናገሩንም የጀመሩት አቶ መለስ ናቸው። ለነገሩ ከደደቢት እስከ ምኒልክ ቤተ መንግሥት የተሰራ የተነገረው ሁሉ የአቶ መለስና የአቶ መለስ ብቻ አንደሆነ ተነግሮን የለ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ወያኔ ሆይ ልብ ግዛ! … ህዝብም በእምቢተኝነቱ ይግፋበት!

የአንባብያን ድምፅ: 4 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Inactive

ያሬድ ኃይለማርያም (ከብራስልስ፣ ቤልጂየም)

ኢትዮጵያ ዛሬ መስቀለኛ መንገድ ላይ ትገኛለች። የወያኔ ግትርነትና መረን የለቀቀ አንባገነናዊነት፣ በሥርዓቱ ተስፋ የቆረጠና የተበሳጨ ሰፊ ህዝብ፣ ለ25 ዓመታት የተጎነጎነ የጎሣ ፖለቲካና ጥላቻ፣ መገለጫ የሌለው ድህነትና ችጋር ሀገሪቱን ሰንገው ይዘዋታል። በአገዛዝ ሥርዓቱ በኩል የሚታየው ህዝብን የመናቅና ከሕግ በላይ የመሆን ዝንባሌ እየከፋ መምጣቱ፤ በሥልጣን ላይ ያሉት ሰዎች አንድም ልባቸው መደፈኑን፤ አለያም ጥልቅ ድንቁርና የተጫጫናቸው መሆኑን ወይም መካር ማጣታቸውን ነው የሚያመላክተው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ለኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ ጥብቅና

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

አንዱዓለም ተፈራ - የእስከመቼ አዘጋጅ

ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱን በግሌ አላውቀውም፤ ነገር ግን እስከሚበቃኝ ድረስ አውቀዋለሁ። ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ እኔን አያውቀኝም፤ ነገር ግን እኔና በሚሊዮን የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዊያን ጠበቆቹ እንዳለን ያውቃል። ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ ጎንደር ውስጥ አንገረብ እስር ቤት ባሁኗ ሰዓት - ምሽት፣ ረቡዕ ሐምሌ ፳፯ ቀን ፳፻፰ ዓመተ ምህረት - ለጊዜው አለ። እዚያ እንዲቆይ ያደረገው ወገኑ ነው። ሁላችንም እንደምናውቀው፤ በእስር ቤት ያለ ግለሰብ፤ በትክክል ይሁን በድፍረት በመታሰሩ ብቻ፤ ጠበቃ ያስፈልገዋል። እናም ጠበቃው ነኝ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ትግሉን ለህዝባዊ ድል ለማብቃት …

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

ፊልጶስ

Ethiopians protest (Oromia & Amhara regions) ህዝባዊ ተቃውሞ በኢትዮጵያ (በኦሮሚያና በአማራ ክልል)

አሁን ያለው ህዝባዊ አመጽ በመላው ሀገሪቱ ለመቀጣጥጠል የበቃው የብዙ ወገኖቻችን ሕይወት ቀጥፎ፣ ለእስር፣ ለስደትና ለምድራዊ ስቃይ ዳርጎ ነው።

የ'ስካሁኑ ትግል ለድል ያለበቃው፤ ወያኔ የፈነጨውና ሀገራችንን እስከማፈራረስ ደረጃ የተቃረበበት ዋና ምክንያት፤ ተደራጅተን የጋራ ኃይል ያለመያዛችንና የወያኔን ማንነት ያለመረዳታችን ነው። ወያኔን መነሻውን፣ አሁን ያለበትንና የአጭር ግዜና የረጅም ግዜ መረኀ ግብሩ ካላወቅነው፤ እንዳለፈው የትግል ዓመታት ሁሉ ዛሬም ርስ በርስ መጠላለፍ ...

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኢትዮጵያ በእሳተገሞራ ጫፍ ላይ ተቀምጣ

የአንባብያን ድምፅ: 4 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Inactive

Quote of Martin Luther King Jr.ፕ/ር አለማየሁ ገብረማርያም  (ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ)

“በሰላማዊ መንገድ ለውጥ እንዳይመጣ የሚከላከሉ ሁሉ ሞገደኛውን እና የማይቀረውን የአብዮት ማዕበል እንዲያስተናግዱ ይገደዳሉ” ጆን ኤፍ. ኬኔዲ

እንዲፈጸምልህ በምትመኘው ነገር ላይ አስቀድምህ ተጠንቀቅ ምክንያቱም የሚሆነው አይታወቅም የተመኘኸውን ልታገኝ ትችላለህና …

በአሁኑ ጊዜ በሕይወት የሌለው እና የህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ (ዘ-ህወሓት) ፈላጭ ቆራጭ መሪ የነበረው አምባገነኑ መለስ ዜናዊ አፈር ይቅለለውና የእርሱን አገዛዝ የማይወዱ ተቃዋሚ ኃይሎች ካሉ ወደ ጫካ በመግባት ተዋግተው በማሸነፍ የእርሱ ወሮበላ የአማጺያን ቡድን እ.ኤ.አ በ1991 እንዳደረገው ሁሉ ሥልጣን መያዝ ይችላሉ በማለት ሰላማዊ ዜጎችን ለኃይል በትምከት አመጽ ይገፋፋ ነበር።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ጠላትን አሳንሶ ማየት፣ የተቃውሞው ጎራ ድክመት

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

ይገረም አለሙ

ታሪካዊው የጎንደር ሰልፍ / People in Gonder are protesting against Ethiopia's ruling party and land grabs, 31 July 2016.

በዚህ ሳምንት በወጣ በአንድ ድርጅት መግለጫ ውስጥ የተመለከትኳት “ወያኔ የበሰበሰ የሳር ጎጆ ነው” የምትል ቃል ከዓመታት በፊት አንድ ወዳጄ ያጫወተኝን አስታወሰችኝ። ወዳጄ ብሔራዊ ወታደር ሆኖ ያሳለፈ ነው። እንደ ዕድል ሆኖ በሠለጠነበት ማሠልጠኛ ውስጥ ተመርጦ ቀርቶ እዛው ነው የአገልግሎት ግዳጁን የተወጣው - ደዴሳ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ