የኢትዮጵያ ምጥ

የአንባብያን ድምፅ: 4 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Inactive

ያዬ አበበ

የሦስተኛው ምጥ አዋላጅ ኢህአዴግ ይሳካለት ይሆን?

ኢትዮጵያ ምጥ ላይ ነች። ከዚህ በፊትም ሁለቴ አርግዛ አዋላጆቿ የሚያደርጉትን ስላላወቁ፤ እናት ብዙ ደም ፈሷት ከሞት አፋፍ ድናለች። የሦስተኛው ምጥ አዋላጅ ኢህአዴግ ይሳካለት ይሆን?

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የወልቃይት ጥያቄ ሕገ መንግሥታዊነት

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

ይገረም አለሙ

Map of "Great Republic of Tigray". "የታላቅዋ ትግራይ ካርታ"

የወልቃይት ጠገዴ ጉዳይ መነሳት የጀመረበት ጊዜ ጠያቂዎቹ እንደሚሉት ከወያኔ የሥልጣን ዕድሜ በላይ ነው። ስሙን ህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ ብሎ፤ ዓላማውን ትግራይን ነጻ ማውጣት አደርጎ የተነሳው ቡድን በለስ ቀንቶት ትግራይን መቆጣጠር ሲችል ቢያንስ በሁለት ምክንያቶች ወደ ቀሪው የኢትዮጵያ ክፍል መስፋፋትን ነው የመረጠው። አንደኛው ምክንያት ማሸነፍ ከተቻለ በትግራይ ሳይወሰኑ ማዕከላዊ ሥልጣን ለመያዝ፤ ሁለተኛው ደግሞ “ነጻ ሊያወጧት የታገሉላትን” ትግራይ ግዛት ለም መሬቶቸን በማጠቃለል ማስፋት ናቸው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ወልቃይት፣ ያሬድ ጥበቡና ጄኔራል ጻድቃን

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

Yared Tibebu. ያሬድ ጥበቡበፍቃዱ ደረጀ

- ጻድቃን እንደ እኛ ሊያስብ ይችላል፣
- ሕጋዊ ማዕቀፎችን እንጠቀም፣
- አዲስ አበባ አድጋለች መጎብኘት ባልችልም፣
- የመለስ ጥሩ ስራ ህወሓትን ከሌሎች ድርጅቶች እኩል አድርጎት መሄዱ ነው

ያሬድ ጥበቡ ኢህዴን የተባለውን ብአዴን ከመሰረቱ ግለሰቦች አንዱ ነበር። ሲታገል ሲታገል ቆየና ከዕለታት አንድ ቀን የዓመት እረፍት ተሰጠው፤ ይህንን የእረፍት ጊዜውን በዋና እንደሚያሰልፍ ቀድሞ የተረዳው ወዲ ዜናዊ፤ ተከዜ ላይ ለምን አንዋኝም ሲል ግብዣ አቀረበለት። ሳያቅማማ ተቀበለው። የመለስ ዜናዊ ጦር እየወጋው ቢሆንም ያሬድ አንዳች ነገር ሳይሰማው ወደ ተከዜ ወንዝ ተጓዘ። እንደደረሱም ጨዋታ ፈረሰ፣ ዳቦ ተቆረሰ። ከዛሬ ጀምሮ የኢህዴን አመራር አይደለህም፤ ሁለት ምርጫዎች አቀረበለት … ብርሀኑ ነጋ የሄደበትን መንገድ መርጦም፤ በፓርት ሱዳን አድርጎ ዲሲ መኖር ከጀመረ 30 ዓመት ሊሞላው የጳጉሜን መጥባት እየተጠባበቀ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በአማራው ክልል ያለው መለስተኛ ጦርነት ሳይባባስ መፍትሔ ይፈለግ

የአንባብያን ድምፅ: 4 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Inactive

ግርማ ካሳ

- በሰሜን ጎንደር ዞን 145 ወታደሮች ተገድለዋል
- ከአዘዞ ካምፕብቻ 143 ወታደሮች ካምፑን ጥለው እስከነ ትጥቃችው ጠፍተዋል

ህወሓት ለሰላም በሮቹን በሙሉ ስለዘጋ፣ በሰላም የሚታገሉ፣ እንደ አንድነት ያሉ ፓርቲዎችን አግዶ፣ እንደ አንዱዋለም አራጌ፣ ናትናኤል መኮንን ኦልባና ለሌሳ … ያሉ ሰላማዊ የፖለቲካ መሪዎችን አስሮ፣ ምርጫ መቶ በመቶ አሸነፍኩ ብሎ፣ ዜጎች ወደ ማይፈለጉት መስመር ፊታቸውን እንዲያዞሩ ገፋፍቷቸዋል። የሰላም በር ሲዘጋ የአመጽ በር ተከፍቷል። በአሁኑ ወቅት ምንም መሸፋፈን አያስፈለግም፤ በተለይም በአማራው ክልል በአሁኑ ጊዜ መለስተኛ ጦርነት ነው ያለው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ለሁሉም ጊዜ አለው

የአንባብያን ድምፅ: 4 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Inactive

ማስተዋል በለጠ

በመላዋ ሀገራችን ለነፃነታችን እየተዋደቁ የሚገኙ ዜጎች ውድ ሕይወታቸውን እየሰው የነፃነት ቀንዲሉን በማብራት ላይ ናቸው። ታሪክ ሲዘክረው የሚኖር ታላቅ መስዋዕትነት እየከፈሉ በመሆናቸው በአልሞ ተኳሽ የወያኔ አጋዚ ጦር አንገታቸው እየታረደና ጭንቅላታቸው እየተገመሰ ሕይወታቸውን የሚያጡ ውድ ወገኖቻችንን ነፍሳቸውን ፈጣሪ ይማርልን።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በኢትዮጵያ ያለው ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓት ነውን? (ክፍል ሁለት)

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

ይገረም አለሙ

በክፍል አንድ ጽሁፌ አንድን ሥርዓት ሕገ መንግሥታዊ ሊያሰኙት የሚበቁ በርካታ ጉዳዮችን ትተን በሕገ መንግሥቱ ላይም የሚነሱ ክርክሮችን አቆይተን ሕገ መንግሥቱ ባለው መልኩ እንኳን የማይከበር አንዳንድ አንቀጾቹም እስከመኖራቸው የማይታወቁ መሆኑ ብቻውን ሥርዓቱን ሕገ መንግሥተዊ ሊያሰኘው እንደማይችል ጠቅሻላሁ። ለዚህ መከራከሪያ ይሆናሉ ያልኳቸውን ጭብጦችም በማንሳት ከሕገ መንግሥቱ አንቀጾች የተወሰኑትን በማስረጃነት ለማቅረብ ነበር የተሰናበትኩት።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ