የማንነት ፖለቲካ ጠንቆችና የአብሮነት አኗኗሪ መፍትሔ ፍለጋ

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

Yussuf Yassin. አቶ ዩሱፍ ያሲንዩሱፍ ያሲን (ደን ሐግ)

"It is NOT our differences that divide us. Rather it is our INABILITY to recognize, accept and celebrate those DIFFERENCES." Audre Lorde

ልዩነቶቻችን ውበታችን የሚሆኑት ስናስተናግዳቸው ብቻ ነው፤ አለበለዚያ ያወዛግቡናል ዩሱፍ ያሲን (አርቲክል 2012)

1. የማንነት ጥያቄዎች በየፈርጁና በየመልኩ

እገሌ የሚባል ስብስብ ለመንግሥት ምክር ቤት የማንነት ጥያቄ አቀረበ። እገሌ የሚባለው ደግሞ በዚህ ክልል ሳይሆን በዚኛው ክልል ልካለል አለ። ሌላው እኛ መታወቂያ መለያ አጠራሬ ይህ ነው እንጂ ይህኛው አይደለም። አንደኛው ብሔረሰብ ልዩ ዞን (ኮንሶ) ሌለኛው ክልል (ሲዳማ) ይሰጠኝ የሚል ጥያቄ አቀረበ። ስብስቦች የማንነት ጥያቄያቸው በሕገ መንግሥት መሠረት ለመንግሥት ምክር ቤት አቀረቡ ሲባል እንሰማለን። ይህንን ጥያቄ ያቀረቡ የቅማነት፣ የቁጫ፣ የወልቃይት፣ የዱቤ ብሔረሰብ አባላት ተገደሉ፣ ታሠሩ፣ ተቀጡ፣ ወዘተ ሲባል እንሰማለን። ገሚሱ የማነት ጥያቄ ቀላል መልስ አለው። ገሚሱ ቀላል መልስ የለውም።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኢትዮጵያዊነት የብሔር/ብሔረሰብ ጥያቄና ፌዴራሊዝም

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

ዶ/ር ፈቃዱ በቀለ

መግቢያ!

አብዮቱ ከፈነዳ ከ1966 ዓ.ም ጀምሮ ህዝባችን ሰላምና እረፍት ማግኘት አልቻለም። አብዮቱ ሲፈነዳ፣ የንጉሳዊ አገዛዝ ሲፈርስ፣ የሱ መሰረት የሆነው የፊዩዳሉ ስርዓት ሲደመሰስ ሰፊው ህዝብ የነፃነት ብርሃንን የማየት ዕድል አጋጥሞት ነበር። እስከተወሰነ ደረጃም ድረስ ነፃነትን በመጎናጸፍ እንደቆመበት የህብረተሰብ ክፍል የየራሱን ማህበራዊ ተቋም መመስረት ችሎ ነበር። ይሁንና ግን ይህ የተጎናጸፈው ድልና የተስፋ ብርሃንን ማየት ከውስጥ ከዚህና ከዚያ ብቅ ባሉ ድርጅቶች፣ ግን ደግሞ ዕውነተኛ ዓላማቸው በማይታወቅ ኃይሎች በመወጠርና ጦርነት ውስጥ እንዲገባ በመገደዱ አገሪቱ እስካሁን ድረስ ጋብ ሊል ያልቻለ ትርምስ ውስጥ እንድትወድቅ ተገደደች።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አበሻው ባንዲራ - ጎንደር ላይ ታየ!!

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

ተስፋዬ ገብረአብ

ታሪካዊው የጎንደር ሰልፍ / People in Gonder are protesting against Ethiopia's ruling party and land grabs, 31 July 2016.

እነሆ! በቅፅል ስሙ "አምባሻው" ተብሎ የሚታወቀው "የኢትዮጵያ ባንዲራ" ባለፈው ሰንበት ማለትም ሐምሌ እሁድ 24 ቀን 2008 ዓ.ም. (ኦገስት 31፣ 2016) ቄሶችና ሼኮች በተገኙበት፣ መቶ ሺህ በሚገመት ህዝብ ሸኚነት የቀብር ሥነሥርዓቱ በበጌምድር ጠቅላይ ግዛት ተፈመ ማለት ይቻል ይሆን? "ምነው ተኛ?" በሚል በሐሜት ድቅቅ አድርገን እንደ ክትፎ ስንከትፈው የሰነበትነው የአማራ ህዝብ ተደራጅቶና ተዘጋጅቶ፣ የቴዎድሮስን ከተማ ሲያንቀጠቅጣት ዋለ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የነፍጠኞች ፖለቲካ

የአንባብያን ድምፅ: 4 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Inactive

ፕ/ር መስፍን ወልደማርያም

ታሪካዊው የጎንደር ሰልፍ / People in Gonder are protesting against Ethiopia's ruling party and land grabs, 31 July 2016.

ነፍጠኛነት ባህላችን ነው፤ ፖለቲከኛነት አዲስና ባዕድ የትግል ዘዴ ነው፤ ፖለቲከኛነትና ነፍጠኛነት ተቃራኒ ተግባሮችን ያመለክታሉ፤ ተቃራኒ ተግባሮች አብዛኛውን ጊዜ ተቃራኒ ዘዴዎች ያስፈልጋቸዋል። ለምሳሌ መፍጨትና ማቡካት ተቃራኒ ተግባሮች ናቸው፤ መፍጨት ሲበታትን፣ ማቡካት ሰብስቦ ያያይዛል፤ የሚፈጭ ሰው ማቡካት ይችላል፤ እንዲሁም ማቡካት የሚችል ሰው መፍጨት ይችላል። ፈጪ አቡኪ መሆን የሚችለውን ያህል ወይም አቡኪ ፈጪ መሆን የሚችለውን ያህል፤ ነፍጠኛ ፖለቲከኛ ወይም ፖለቲከኛ ነፍጠኛ መሆን ይችላል ወይ? መልሱ ግልጽ ነው፤ አይችልም። የነፍጠኛ ትግል በጠመንጃ ነው፤ የፖለቲከኛው ትግል በቃላት፣ በንግግር ነው። በሌላ አነጋገር የነፍጠኛ በዱላ፣ የፖለቲከኛ ትግሉ በመላ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ታሪካዊው የጎንደር ሰልፍ እና እንድምታው

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

ክንፉ አሰፋ

ታሪካዊው የጎንደር ሰልፍ / People in Gonder are protesting against Ethiopia's ruling party and land grabs, 31 July 2016.

በሰሞነኛው የአዲስ አቤ ቀልድ ልጀምር። ወጣቱ፣ ሱሪ ለመግዛት ወጥቶ አንድ የልብስ ሱቅ ወስጥ ገባ። ባለ ሱቁ ጠየቀው። “የቻይና ይሁንልህ ወይንስ የአውሮፓ ሱሪ?” ወጣቱም መለሰ። “የለም የለም ... የጎንደሩን ሱሪ ነው የምፈልገው።”

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ህወሓት የተከለውን የጡት ቆረጣውን ሐውልት አፍርሰን እንጣለው

የአንባብያን ድምፅ: 4 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Inactive

ዓሊ ጓንጉል

“... ሃያዎቹ መጨረሻ ላይ ያለ፣ በፊቱ የተደፋ፣ እጆቹን ወደፊት ዘርግቶ፣ ... ልብሱ በደም እና አቧራ የጨቀየ ኢትዮጵያዊ ... አስከሬን መንገድ ዳር ወድቋል፣ ሰውየው ጫማ፣ ገንዘብ፣ መታወቂያ የለውም። ለአርብ ጸሎት የሚሄዱት ሰዎች በሚያዩት አዝነዋል፣ ግን የገረማቸው አይመስሉም ...” ይህ በትናንትናው ዕለት (august 31/2016) በኒውስዊክ መጽሔት ላይ ከወጣ የዜና ዘገባ የተወሰደ ነው። ርዕሱ “ጦርነትን የሸሹ የመናዊያን እና ድርቅን የሸሹ ኢትዮጵያዊያን ጅቡቲ ላይ ተገናኙ” ነው የሚለው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ