የጎንደሮች ትግል የኢትዮጵያ ህዝብ ድል

የአንባብያን ድምፅ: 4 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Inactive

አብርሃም በየነ

የጎንደር አመጽ Protest in Gonder July 31, 2016

የጎንደሮች የመለከት ድምፅ ኢትዮጵያ ነች። የእምቢልታው መስተጋቦ ኢትዮጵያዊነት ነው። የጥሩምባው የክተት ጥሪ የአማራው ህዝብ የህልውና ጥያቄ ነው። ስለሆነም አማራ ለህላዌው፣ ኦሮሞ ለመብቱ፣ ጋምቤላ ለመሬቱ፣ አፋር ላንድነቱ በጠላቱ በወያኔ ላይ የተነስ ጥሪውን ተቀብሎ በጋራ እንዲያምጽ ነጋሪቱ ተጎሹሟል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኢትዮጵያ የፌደራል ሥርዓትን የምትከተል ሀገር አይደለችም

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

ገለታው ዘለቀ

ኢትዮጵያ ሆይ የአስተዳደር ዘየሽ ምን ይመስላል? ተብላ ብትጠየቅ በዓለም ላይ የፌደራል ሥርዓትን ከሚከተሉ ሀገራት አንዷ ነኝ ስሜም የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግሥት ይባላል ትላለች። በርግጥ በዓለም ላይ ካሉ ብዙዎቹ ሀገራት የፌደራል ሥርዓትን አይከተሉም። ብሪታኒያን ፈረንሳይን ጨምሮ በዴሞክራሲ የበለጸጉ አንዳንድ ሀገራት የአሃዳዊ አስተዳደር ዘየን ይከተላሉ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አስቸኳይ ወቅታዊ መልዕክት!

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

ነፃነት ዘለቀ (ኢትዮጵያ)

አሁን ያለንበት ወቅት ለወሬና ለፍልስፍና አመቺ አይደለም። በሞቀንና በበረደን ቁጥር ከያለንበት ሸጥና ጎጥ እየተነሣን በብዕርም ይሁን በአንደበት የምንወራከብበት ወይም እንካስላንትያ የምንገጥመት ወቅት ላይ አይደለንም። ጊዜው የጣር መጨረሻ ነው፤ ዘመኑ የነፃነት ትግል ወቅት ነው። ስለሆነም ከሚያናቁረን ይልቅ የሚያስማማንን ንግግርና ሃሳብ የምንወረውርበት ሊሆን ይገባል። ከእልህና ከስድብ ይልቅ መቻቻልና መግባባት የሠፈነበት የመጨረሻ ምዕራፍ ሊሆን ጊዜው ግድ ይለናል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ምላሽ ለሌ/ጄ ፃድቃን ገ/ተንሳይ “የሀገራችን ፖለቲካ ሁኔታና የመፍትሔ ሃሳቦች” ጽሁፍ

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

ለመፍትሔው መፍትሔ የወያኔ/ህወሓትን ዕድሜ ለማራዘም በሌ/ጄ ፃድቃን ገ/ተንሳይ የመፍትሔ ሃሳቦች

(የሌ/ጄ ፃድቃን ገ/ተንሳይን ጽሁፉ ለማንበብ እዚህ ይጫኑ!)

ነሲቡ ስብሐት፤ ከሰሜን አሜሪካ

ሌ/ጄ ፃድቃን ገ/ተንሳይን

እነሆ 17 ዓመት በበረሃ 25 ዓመት በመንግሥት ሥልጣን የተቆናጠጠው ወያኔ ዛሬ የሥልጣን ዘመኑ ማብቂያው የመጨረሻው መጀመሪያ ላይ ደርሷል። በትግሉ ላይ ነበርን ብቻ ሳይሆን በከፍተኛ አመራር እርከን ላይ ነበርን የሚሉ የወያኔ ባለሥልጣን፤ የድርጅታቸውን 17 ዓመት የትግል ጉዞ አብረው ፕሮግራም ሲነድፉ፣ ፖሊሲ ሲያወጡ፣ የትግራይ ነፃ አውጪ ብለው በዘር ሲደራጁ፣ የአማራ የበላይነት ሰፍኗል ብለው አማራ ላይ ሲያነጣጥሩ፣ የብሔር/ብሔረሰቦች መብት እስከመገንጠል ብለው የዘር ፖለቲካ ሲያራምዱ፣ ኤርትራ በኢትዮጵያ ቅኝ ተይዛለች ብለው ከሻዕቢያ ጋር ለኤርትራ ነፃነት ሲታገሉና ሲያታግሉ የነበሩ ዋናው የድርጅቱ አመራር ባልደረባ፤ ዛሬ የወያኔ ወንበር እንዳበቃለት ሲገለጥላቸው “ዕድሜውን እንዴት እናራዝመው?” “ትንታኔአቸውን” አስነብበውናል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የሀገራችን ፖለቲካዊ ሁኔታና የመፍትሔ ሃሳቦች (ሌ/ጄ ፃድቃን ገ/ትንሳኤ)

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

ሌተናል ጄኔራል ፃድቃን ገ/ትንሳኤ

ሌተናል ጄኔራል ፃድቃን ገ/ትንሳኤ Photo – General Tsadkan during an interview with HornAffairs. Feb. 2015

መግቢያ

ከሃያ አምስት ዓመት ኢህአዴግ የደርግን መንግሥት በጦርነት አሸንፎ የሀገራችንን ፖለቲካዊ ሥልጣን ከተቆጣጠረ በኋላ፤ ቀስ በቀስ እያደጉ የመጡ ፖለቲካዊ ችግሮች በግልፅ ጎልተው መታየት ጀምረዋል። አሁን ገዥው ፖርቲና ፖርቲው የሚመራው መንግሥትም የችግሮቹን መኖር አምኖ ለመፍታት እየተንቀሳቀሰ እንደሆነ መንገር ከጀመረ ሰነባብቷል። ይህ ሁኔታ ለማንኛውም የሀገሩን ደህንነትና ሰላም፤ ቀጣይነት ያለው ኢኮኖሚያዊ ዕድገትና ማህበራዊ ብልፅግና፤ ለሚመኝ ሀገር ወዳድ ዜጋ ያሳስባል። ከዚህ አንፃር የተለያዩ አስተያየቶች እየተደመጡ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

“ከዚህ በላይ ምን ትሆናለህ? ክተት! አትነሳም እንዴ?” አለ ዘረኛው ኒዮ ፋሺስት ዶናልድ ትራምፕ በሪፑብልካኑ ጉባዬ ላይ

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

ፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም (ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ)

Trump

በጁሊየስ ቄሳር ተውኔት ውስጥ የቄሳርን ሞት ተከትሎ ጣሊያንን ሽባ የሚያደደርግ የእርስ በእርስ ጦርነት ሊከሰት እንደሚችል ሸክስፒር የማርክ አንቶኒን ገጸ ባህሪነት በመላበስ እንዲህ በማለት አስጠንቅቀው ነበር፤

“…እናም አቴ በእርሱ በኩል ከጋነም እሳት ሆኖ በመምጣት የቄሳርን መንፈስ በመላበስ የንጉሱን ድምጽ በመያዝ ለበቀል ተዘጋጅቷል። እናም እናልቅስ፣ እናም እነዚህን የጦርነት ውሾች እናስወግድ“ ብለው ነበር።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ