የተባበሩት መንግስታት ድርጅት፣ ወያኔ እና የሚዘረፈው ሰራዊት

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

መሳይ መኮንን

ዛሬ ለኢሳት የደረሰው ጥብቅ መረጃ 11ዓመታትን ወደ ኋላ በትዝታ ወሰደኝ። ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት ከዋናው ጸሀፊ ቢሮ አፈትልኮ የወጣው መረጃ እንደሚያጋልጠው ለሰላም አስከባሪ 11 ሺህ የኢትዮጵያ ሰራዊት የሚከፈለው ደምወዝ ከ90 በመቶ በላይ የህወሀት ካዝና ውስጥ የሚገባ ነው። በወር 13 ሚሊዮን ዶላር(500 ሚሊዮን ብር ገደማ) የወታደሩን ገንዘብ ህወሀቶች ይቀራመቱታል። ይህን ጉዳይ የመንግስታቱ ድርጅት የሚያውቀው ይመስለኛል። ለዚህም እኔ የተሳተፍኩበትን የሰላም አስከባሪ ዘመቻ አጋጣሚ በአስረጂነት ማሳየት እችላለሁ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የአዲሱ ህወሓት መንግሥት መጥፎ አጋጣሚ

Star InactiveStar InactiveStar InactiveStar InactiveStar Inactive

ኤርሚያስ ለገሠ (ክፍል-1)

1 - ደስታ እና ሀዘን

ሰሞኑን ፍቺ በፍቺ ሆነናል። የዞን ዘጠኝ ጦማሪያን ከፊል አካል ተፈታ። ደስ አለን። የተፈቱት ካልተፈቱት ያላቸው ልዩነት ለብዙዎች ግራ ቢያጋባም!…ዛሬ ደግሞ እነ ሀብታሙ አያሌው ተፈተዋል። ይህም በግለሰብ ደረጃ ደስ የሚል ዜና ነው። ቢያንስ በቅርብ የማውቀው ሀብታሙ (” ሀብትሽ!”) ክፋ ደጉን የማታውቀው ልጁ እጁ ላይ ስታንቀላፋ፣ ወደ አልጋዋ ወስዶ ሲያስተኛት፣ ከእንቅልፏ ስትነቃ አቅፎ ሊያነሳት በመቻሉ ደስ ይለኛል። እንኳን ለዚህ አበቃህም ማለት እፈልጋለሁ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኦባማ የአፍሪካን ገዢዎች እያዋዛ ደቆሳቸው!

Star InactiveStar InactiveStar InactiveStar InactiveStar Inactive

ፕ/ር መስፍን ወልደ ማርያም

ኦባማ በአፍሪካ ኅብረት ያደረገው ንግግር ብዙ ጥያቄዎችን መልሷል፤ የኦባማ ጉብኝት ያስከተለው ጫጫታ ሁሉ መልስ አገኘ፤ የሰው ልጆች በመሀከላቸው ምንም ዓይነት የአድልዎ ልዩነት ሳይደረግባቸው በሰውነታቸው ብቻ በተፈጥሮ ያገኙትን ክብራቸውንና መገሣቸውን አስከብረው መኖር እንዳለባቸው በአጽንኦት ተናገረ፤

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ዝዋይ እስር ቤት

Star InactiveStar InactiveStar InactiveStar InactiveStar Inactive

ፕ/ር መስፍን ወልደማርያም

ሐምሌ 16/2007 ዓ.ም. ለአሥር ወራት በእስር ላይ የቆየውን ጋዜጠኛ፣ ተመስገን ደሳለኝን (ከኃይለ ማርያም ደሳለኝ ጋር ዝምድና የለውም፤) ለመጠየቅ ወደዝዋይ ወህኔ ቤት ሄጄ ነበር፤ የወሕኒ ቤቱ ባለቤቶች ማረሚያ ቤት ይሉታል፤ ማረሚያ ቤት ማለት ሀሳቡን በነጻነት የሚገልጽና በሀሳቡም ከወያኔ ጋር በሎሌነት ለመተዳደር የማያመች ሲሆን የቀናውን በጉልበት የሚያጎብጡበት ማለታቸው ነው፤ ማረም ማለት ቀጥታውን ማጉበጥ ነው፤ እንዴት እንደሚያጎብጡት ላሳያችሁ፤--

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በበጋው ወር ፍራንክፈርት ትጣራለች

Star InactiveStar InactiveStar InactiveStar InactiveStar Inactive

ዮሃንስ ደሳለኝ (ፍራንክፈርት - ጀርመን)

መቼም ማንም ልብ እንደሚለው ሞቃታማው የሐምሌ ወር ገና ብቅ ሲል ነው ጀርመናውያን በበጋ አለባበስ ደምቀው የሚታዮት።

የዘንድሮው በጋ (sommer, auf Deutsch) ወር ገና ሰኔ አጋማሽ ለይ ነበር ወበቁን የጀመረው ፣ ቀኑ እየጨመረ ወደ ዋናው በጋ ሲገባ ነዋሪውም የአለባበስ ሁኔታውን ከዕለቱ አየር ሁኔታ ጋር እየቃኘ ስያስኬደው አጀብ ያሰኛል ፣ አንዳንዶቹማ ከወገብ በታች ለመከለል ሲባል ብቻ ከሚጠለቅ አልባሳት ውጭ የላይኛውን የሰውነት ክፍል ማራቆት የለመዱትና የግድ የሆነ ድርጊት ነው፣ አሊያ ግለቱ እንኩዋን በልብስ በእርቃንም አቅል ያስታል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የነጻነት ትግል መጀመሪያው የቀና ልቦና ባለቤትነት ነው

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

Magdalaወለላዬ ከስዊድን

አፄ ቴዎድሮስ ያሠሩትን መድፍ (ሴባስቶፖል) ወደ ተራራው አናት ለማውጣት እየተጣደፉ ነው። እሳቸው ጭምር በጉልበት እያገዙ ሲገፋ ውለው ረፋዱ ላይ ከሰፈር ደርሰው ሲመለሱ አንዱ መድፉን ከሚገፉት ተለይቶ ወደ ሰፈር ሲወርድ መንገድ ያገኙትና ቆም ብለው ወዴት ነው ሥራ ትተህ የምትሄድ? ብለው ይጠይቁታል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ