የወያኔ የሩብ ምዕተዓመት ሥልጣንና ፀረ−ወያኔው የትግል ጉዞ

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

በቀለ ደገፋ (ከኦስሎ፣ ኖርዌይ)፣ ጳጉሜን 2009 ዓ.ም.

ሕወሓት/ወያኔ
ለ26 ዓመታት ሥልጣንን የሙጥኝ ይዞ ያለው ወያኔ/ሕወሓት

ወያኔ ሥልጣንን የሙጥኝ ይዞ አገራችንንና ሕዝቧን ቁም ስቅል ማሳየት ከጀመረ እነሆ 26 ዓመታት ተቆጠሩ። ከጀሌዎቹና ፍርፋሪ ከሚበትንላቸው አጨብጫቢዎቹ ያለፈ እዚህ ግባ የሚባል የሕዝብ ድጋፍ ሳይኖረው፤ ይልቁንም በሕዝብ ተጠልቶና ተተፍቶ ከሩብ ምዕተዓመት በላይ ሥልጣን ላይ የመቆየቱ ነገር እንቆቅልሽ የሆነባቸው እጅግ በርካታ ናቸው። በአንፃሩ ሥርዓቱን ለማስወገድ በተለያየ አቅጣጫ የሚደረገው ትግል ውጤት አልባ መሆን ተስፋ አስቆርጧቸው የወያኔ ከወንበሩ መነሳት የማይታሰብ እንደሆነ የደመደሙም አልጠፉም።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኢትዮጵያውያን ብቻ የሚያስወግዱት አረም

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

አብራሃም ለቤዛ

አረም
ወያኔ የተሰኘው አረም በአፋር፣ እንቦጭ ደግሞ በጣና ኃይቅ

እንቦጭን ከጣና ወያኔን ከአፋር ላይ ነቅለን የጣልን ለት፤
የባህርዳር ፈርጥሽ የአፋር ገሞራ አለት፤
ታትሞ ይቀራል በዓለም-አቀፍ መዝገብ ይሆናል ቅርስ ውበት፤
መቼ ይጎልና አሳውም ከጣና በከል ወተቱ አፋር ቤት፤
ሕብረታችን ይታይ አንዱ ለአንዱ ይድረስ፤
ዋጋ ያስከፍላል መታገስ እኛ ዘንድ አስቲደርስ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ዘረኝነት የወያኔ መጠባበቂያ ካርድ

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

ይገረም አለሙ

ሰሚ ጠፍቶ እንጂ- እዛም እዚህም ሰፈር

ቀድሞ የገባቸው አስጠንቅቀው ነበር፤

ለሁሉም አይቀሬ የሆነውና ክፉ ደግ ሀብታም ድሀ ምንዝር ባለሥልጣን ሳይልና ሳይለይ እኩል የሚወስደው ሞት በቅርቡ የነጠቀን አቶ አሰፋ ጫቦ ከመገናኛ ብዙሀን ጠፋ ብለው ሰነባብተው አላስችል ብሎአቸው ብቅ ሲሉ ትቼው ረስቼው አንደሚሉት መተው ሆነ መርሳት ይቻል ከሆነ ብዬ ልሞክር ጠፋ አልኩና አላስችልህ ብሎኝ እነሆ ብቅ አልኩ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በገጠር የሚኖረው የሸዋ ኦሮሞ ከከተሜው ጋር እድል ፈንታው የተጣበቀ ነው

የአንባብያን ድምፅ: 4 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Inactive

ግርማ ካሳ

ከአራት መቶ ዓመታት በፊት የነበረችውን ኢትዮጵያ የሚያሳዩ ካርታ
ከአራት መቶ ዓመታት በፊት የነበረችውን ኢትዮጵያ የሚያሳዩ ካርታ። በካርታው እንደምናየው ሸዋ የሚባል አካባቢ መሐል ላይ እናያለን። በምዕራብ ወሎም “አምሃራ” የሚባል ቦታም ነበር። ግን በጣም ትንሽ ቦታ ነበር፤ አሁን አማራ የሚባለው አልነበረም። ኦሮሚያ የሚባለው አንድ ቦታ አይታይም።

አዲስ አበባንና በዙሪያዋ ያሉ የሸዋ ዞኖችን ያካተተ አዲስ ክልል የመኖሩን አስፈላጊነት በተመለከተ ከዚህ በፊት አንዳንድ ጽሁፎችን ለንባብ ማብቃቴ ይታወቃል። ለደረሱኝ በርካታ የድጋፍና የማበረታቻ መልዕክቶች ያለኝም ምስጋና ለማቅረብ እወዳለሁ። በርካታ ጸሐፊያንም የሸዋን ክልል አስፈላጊነት መጻፍና ግፊት ማድረግ መጀመራቸውም አስደሳች ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ቀይ ባህር የኢትዮጵያ ወይስ የማንም መራኮቻ?

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

አብራሃም ለቤዛ

Ethiopian Navey
የኢትዮጵያ ባህር ኃይልና ቀዳማዊ ኃይለሥላሴ

ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤት በነበረችበት ጊዜ በቀይ ባህር ላይ ያላትን ቁጥጥር ዓለም አቀፍ ተቀባይነት የጎላ ነበር። በኢትዮጵያ ጂኦፖለቲካል አቀማመጥ ምክንያት እና ምስጋና ለነገሥታቶቾ ታሪካዊ የባህር በር ባለቤትነትዋን አስከብረው ቢያልፉም፤ ይኽ ትውልድ ግን የተረከበውን አደራ መጠበቅ አልቻለም።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በአዲስ አበባ ላይ የልዩ ተጠቃሚነት መብት ድንጋጌ ይዘት እና አንድምታው

የአንባብያን ድምፅ: 4 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Inactive

መንበሩ ከመሃል አራዳ

Bole, Addis Ababa
ቦሌ ሰፈር፣ አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ

ወያኔዎች ሥልጣን ላይ በቆዩባቸው አመታት ያጋጠማቸውን ፈተና ከሚወጡባቸው ስልቶ አንዱ፣ አዲስ አጀንዳ ፈጥሮ የፖለቲካ ተቃወሞውን ትኩረት ማስቀየር ነው። የሚገርመው ነገር ይህ ዘዴ የሥርዓቱን አድሜ በማስቀጠል ስኬት ብቻ ሳይወሰን፣ በግራም በቀኝም ያለው የተቃዋሚ ወገን፣ መሰረታዊውን የሥርዓት ለውጥ ጥያቄውን ረስቶ፣ ሙሉ ቀልቡን ወያኔ በተወረወረለት አጀንዳ ላይ በመራኮት፣ እርስ በርስ እየተባላ የትግል ግዜውን ያባክናል። ባለፈው አንድ ዓመት መጠነ ሰፊ የሕዝብ ተቃወሞ ያደናገጠው ወያኔ፣ ለመሰረታዊው ጥያቄ መልስ ሳይሰጥ፣ በልዩ ጥቅም መብት ሽፋን አዲስ የማደናገሪያ አጀንዳ ይዞ ብቅ ብሎአል። ለእሩብ ክፍለ ዘመን ያህል ሲሰራበት የነበረውን የከፋፍለህ ግዛው ስልት ያልተገለጸላቸው አንዳንድ ጽንፈኛ ወገኖች (ethno-chauvinist) ከወያኔ የተወረወረውን አቅጣጫ ማስቀየርያ አጀንዳ በመቀበል፣ ከሥርዓቱ የበለጠ በማስተጋባት ላይ ይገኛሉ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ