ኳስ እና የ"ቦይኮት" ፖለቲካ

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

ክንፉ አሰፋ

Gosaye Tesfaye
ድምጻዊ ጎሳዬ ተስፋዬ

በዘንድሮው የሰሜን አሜሪካ እና የአውሮፓ ስፖርት እና ባህል ፌስቲቫሎች ላይ የቦይኮት (እቀባ) ዘመቻዎች ተነስተው ነበር። የዘማቻዎቹን ውጤቶችም አይተናቸዋል። በዚች አጭር ጽሁፌ የማተኩረው በውጤቶቹ ላይ አይደለም። በሲያትሉም ሆነ በሮም ዝግጅቶች ላይ ስለነበርኩ፤ የቦይኮት ዘመቻዎቹ ከጅምሩ ጥቅም እና ጉዳቶችን አመዛዝነው ነበር ወይ? የሚለውን በጥቂቱ ለመፈተሽ እሞክራለሁ። በዚህ ርዕስ ላይ ስጽፍ አዋራ እንደሚነሳ አምናለሁ። በጉዳዩ ላይ እጅግ ብዙ ሰዎች ሲወያዩ ብታዘብም በፍርሃት ይሁን በሌላ ምክንያት ሃሳባቸውን በአደባባይ ለመናገር ግን ሲደፍሩ አይታይም።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የሱሌይማን ደደፎ ደብዳቤ

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

ኤርሚያስ ለገሰ

ሱሌይማን፣ ክንፈና ቴድሮስ
አምባሳደር ሱሌይማን ደደፎ፣ ብ.ጄ/ል ክንፈ ዳኘውና ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም (ከግራ ወደቀኝ)

በሕወሓቱ ጄኔራል ክንፈ ዳኘው ስለሚመራው የመከላከያ ብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፕሬሽን (ሜቴክ) ሌብነት እና ዝርፊያ ብዙ ተብሏል። ዕድሜ ይስጠን እንጂ ለወደፊቱም እጅግ በጣም ብዙ ይባላል። በትክክልም ይህ በእውቀት አልቦነት እና ማን አለብኝነት የሚንቀሳቀስ ኮርፖሬሽን በአንድ በኩል የአገሪቱ መፃኢ እድል እያጨለመ፣ በሌላ በኩል የሕወሓት የግል ንብረት የሆነውን ኤፈርት የፋይናንስ አቅም እያደለበ እንዲሄድ በማድረጉ ምክንያት ጊዜ አጥፍቶ መነጋገሩ ቢያንስ ከህሊና ተጠያቂነት የሚያድን ይሆናል። ዘለግ ባለ ሁኔታ መነጋገሩ ፍሬ ካፈራ ደግሞ የሕወሓቶችን የዘረኝነት አምድ ለማፈራረስ፣ የአገር መግደያ ኃይላቸውን ለመደምሰስ እና የአፓርታይድ መሰል ፖሊሲና አካሄዳቸውን ለመግታት የሚረዳ ይሆናል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የኦሮሞ አክራሪዎችና እኛ

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

ግርማ ካሳ

Geez
በተለምዶ ግዕዝ ፊደል ተብሎ የሚጠራው የሁሉም ኢትጵያያውያን ፊደል

የተከበሩ የቀድሞ የፓርላማ አባል አቶ ግርማ ሰይፉ ማሩ (የመርካቶ ልጅ፣ ኩሩ የኦሮሞ ኢትዮጵያዊ ብሔርተኛ) እንዲህ ብለው ጦመሩ፤

“እነዚህ ትምህርት ቤቶች (በአፋን ኦሮሞ የሚሰጡ) በጥራት ትምህርት ሊሠጡ የሚችሉት በኦሮሚያ መስተዳድር አዲስ አበባ ውስጥ የሚሰሩ ሰራተኞች በሙሉ፣ እንዲሁም በፌዴራል መንግሥት ውስጥ የሚሰሩ የኦሮሞ ተወላጅ የሆኑ እና የዚህ ፖሊሲ ደጋፊ ሰራተኞች ቢቻል በፈቃደኝነት ካልሆነ ግን በግድ ሁሉም ልጆቻቸውን እነዚህ ትምህርት ቤቶች ውስጥ መላክ እንዳለባቸው ይሰማኛል”

“ፊንፊኔ የሚለውን ቃል ቦይኮት ማድረግ ያለብን ይመስለኛል” (አዲስ አበባን ፊንፊኔ ማለቱ)

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አፋን ኦሮሞ የኢትዮጵያ የሥራ ቋንቋ የመሆን ግዴታነትና የራሱ በሆነው በኢትዮጵያ ፊደል የመገልገል ተገቢነት

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

አብርሃም ቀጀላ

Geez
በተለምዶ ግዕዝ ፊደል ተብሎ የሚጠራው የሁሉም ኢትጵያያውያን ፊደል

ከጥንት ጀምሮ አስቀድሞ በሀገረ ኢትጵያያ ላሉት የሕዝብ ቋንቋዎች ሁሉ በምልአት፣ በጥራትና በብቃት ሲያገለግል የነበረው፤ በተለምዶ ግዕዝ ፊደል ተብሎ የሚጠራው የሁሉም ኢትጵያያውያን ፊደል እ.ኤ.አ በ1983 ዓ.ም. በመንግሥት መለዋወጥ ተፈጥሮ በነበረው ክፍተት ጥቂት ግለሰቦች በፖለቲካ ስሜታዊነትና ግልፍተኝነት ወደፊት በቀጣዩ ሕዝቦች ላይ የሚያመጣውን ጣጣ፣ መዘዝ፣ ጉዳት እና ቀውስ ሳያጤኑ የቀድሞ ያለፈው ፖለቲካዊ ችግር በፈጠረው ቁጣና ትኩሳት ብቻ በመነዳት አፋን ኦሮሞ ግእዙን እንዲተው አድርገዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ነገሪ ሌንጮ፦ አቦይ ስብሃት በሙስና መታሰራቸውን ይንገሩን

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

ክንፉ አሰፋ

ዶ/ር ነገሪ ሌንጮ
ዶ/ር ነገሪ ሌንጮ፣ የኢትዮጵያ የመንግሥት ኮምዩኒኬሽንስ ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ሚኒስትር

የነጋዴዎች አድማ ዛሬም እንደቀጠለ ነው። ገዥው ፓርቲ ከየአቅጣጫው በመወጠሩ - የችግሩን ትኩረት አቅጣጫ ማስቀየር አለበት። የተለመደ የፉገራ ካርዳቸውን መዘዝ አድርገው ለዶ/ር ነገሪ ሌንጮ ሰጡዋቸው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የግብሩ አመጽ - የፍጻሜው ጦርነት

የአንባብያን ድምፅ: 4 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Inactive

ክንፉ አሰፋ

አገሬ ሲኦል ኾናብኛለች
"አገሬ ሲኦል ኾናብኛለች" ሕዝብ

የአስቸኳይ (የአፈና) ግዜ አዋጁ ገና አልተነሳም። በአዲሱ የግብር ትመና ሳብያ ከዳር እስከዳር የተነሳው ሕዝባዊ አድማ እና አመጽ ግን አዋጁን ውድቅ ያደረገው ይመስላል። አንድ ሥርዓት ራሱ ያወጣው ህግ በሕዝብ ሲሻርበት - ያኔ ነው ያበቃለት!

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ