አነጋጋሪው የፕ/ር ፍቅሬ ቶሎሳ መጽሐፍ ምጥን ዳሰሳ (ክፍል ሁለት)

መንግሥቱ አበበ

• የአማራ፣ የትግሬ ወይም የኦሮሞ ስርወ - መንግሥት ኢትዮጵያ ውስጥ አልነበረም
• “ምኒልክ ጡት ቆርጠዋል” ብለው ሀውልት ያቆሙ በድርጊታቸው ማፈር አለባቸው
• በ21ኛው ክፍለ ዘመን የግዕዝ ፊደላትን ጠልተን ላቲን ፍለጋ የሄድንበት ምክንያት
ምንድን ነው?

"የኦሮሞ እና የአማራ እውነተኛው የዘር ምንጭ" ፕ/ር ፍቅሬ ቶሎሳ

(ካለፈው የቀጠለ)
ባለፈው ሳምንት “አነጋጋሪው የፕ/ር ፍቅሬ ቶሎሳ መጽሐፍ ምጥን ዳሰሳ” በሚል ርዕስ ደራሲው “የኦሮሞና የአማራ እውነተኛ የዘር ምንጭ” በማለት ለንባብ ባበቁት አዲስ መጽሐፍ ላይ የተደረገ ምጥን ዳሰሳ ማቅረባችን ይታወቃል። ቀሪውን ክፍል እነሆ፡- (ክፍል አንድን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ!)

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የፕ/ር ፍቅሬ ቶሎሳ መጽሐፍና የኢትዮጵያ የወደፊት ዕጣ ፈንታ

ተክለብርሃን ገብረሚካኤል

"የኦሮሞ እና የአማራ እውነተኛው የዘር ምንጭ" ፕ/ር ፍቅሬ ቶሎሳፕ/ር ፍቅሬ ቶሎሳ ”የኦሮሞና የአማራ እውነተኛ የዘር ምንጭ” በሚል ርዕስ በሐምሌ ወር 2008 ዓ.ም. አሳትመው ያወጡት መጽሐፍ በኢትዮጵያ ታሪክ ምርምርና ጥናት አዲስ ፈር ቀዳጅ ለመሆኑ ብዙ ማስረጃዎችን ማቅረብ ይቻላል። አንደኛ የኦሮሞ ሕዝብ ከኢትዮጵያ ውጪ (ከማዳጋስካር፣ ከኢስያ ክፍሎች) ወደ ኢትዮጵያ ፈልሶ የገባ ሲባል የኖረውን አፈ ታሪክ አሳማኝ ናቸው በሚባሉ ማስረጃዎች አስደግፈው ከእውነቱ የራቀ መሆኑን አሳይተዋል። ሁለተኛ አማራ የገዥ መደብ ተብሎ በአማራ ሥርወ መንግሥት ኦሮሞን ጨምሮ ሌሎች የባህል ገጽታዎቹን በኃይል ጭኖባቸዋል የሚለው ውግዘት ምንም ታሪካዊ መሠረት እንደሌለውና እንዲያውም፣ በአግአዚ/ሰሎሞናዊና በዛጉዌ ሥርወ መንግሥታት በንጉሠ ነገሥትና ደረጃ አማሮች የበላይነት ይዘው እንደማያውቁና ይልቁንም በዚህ የሥልጣን ደረጃ አብዛኞቹ ኦሮሞዎች እንደነበሩ አረጋግጠዋል። በተጨማሪም በዘመነ መሳፍንት በባለሙሉ ሥልጣን እንደራሴነቱ በኢትዮጵያ ሥልጣን ይቀራመቱ የነበሩት አማሮች ሳይሆኑ፣ በተለይ የየጁ ኦሮሞዎች መሆናቸውን ቁልጭ አድርገው ፕ/ር ፍቅሬ ቶሎሳ አመልክተዋል። ሦስተኛ አማሮች የዘር ምድባቸው ሴማዊ (ሴሜቲክ) ሳይሆን እንደ ኦሮሞ ኩሻዊ መሆኑን፣ ሁለቱም ጎሳዎች (ጎሳ በቋንቋ መወሰኑን አመልክተዋል) የኢትዮጵያውያን ሁሉ ጥንታዊ አባት ከሆነው ኩሻዊው ኢትዮጵያ ልጅ ከደሽት (ከደሴት) የመጡ መሆናቸውን ጠቁመው፣ ጂኦግራፊያዊ ወይም መልክዓ ምድራዊ ምንጫቸው ዛሬ ጐጃም እየተባለ የሚጠራው አካባቢ መሆኑን አመልክተዋል። እነዚህ ሁሉ አዳዲስ ታሪካዊ ግኝቶች ናቸው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አነጋጋሪው የፕ/ር ፍቅሬ ቶሎሳ መጽሐፍ ምጥን ዳሰሳ (ክፍል አንድ)

መንግሥቱ አበበ

- የኦሮሞና የአማራ ህዝብ በደምና ስጋ ብቻ ሳይሆን በባህል፣ በኅሊናና በመንፈስ ዳቅሏል፤ ተዋህዷል
· አንዳንዶች፤ “አፄ ምኒልክ ጡት ቆረጡ፤ 5 ሚሊዮን ኦሮሞ ገደሉ” እያሉ የሚነዙት የሐሰት ፕሮፓጋንዳ ነው
· አማራውን እወክላለሁ ብሎ ያወጀ ንጉሠ ነገሥትስ ይኖር ይሆን?

"የኦሮሞ እና የአማራ እውነተኛው የዘር ምንጭ" ፕ/ር ፍቅሬ ቶሎሳ

ነዋሪነታቸው በአሜሪካ የሆነው ፕሮፌሰር ፍቅሬ ቶሎሳ ጂግሳ፤ በቅርቡ የኦሮሞ የአማራና የተቀረው የኢትዮጵያ ህዝብ እውነተኛና ትክክለኛ የዘር ምንጭ ምን እንደሆነ ከ5ሺ ዓመታት በላይ ወደኋላ ተጉዘው፣ ማስረጃ አስደግፈው፣ ምንጭ ጠቅሰው፣ እስካሁን ድረስ የምናውቀውን የኢትዮጵያን ታሪክ የሚሽር፣ አዲስ የኢትዮጵያ ታሪክ በዝርዝርና በጠራ አቀራረብ የሚገልጽ ድንቅ መጽሐፍ አቅርበዋል። እስካሁን የነበረውን ታሪክ ከስር መሰረቱ ገለባብጦ፣ በአዲስ ታሪክ የሚተካ መጽሐፍ አግኝቼና አንብቤ አላውቅም፤ስለዚህም በጉጉት ነው ያነበብኩት።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የኢትዮጵያ ባለውለታዎችና ጀግኖቻችን የተዘከሩበት

የ“ኢ/ር ታደለ ብጡል የሕይወት ታሪክ አርኣያነት” መጽሐፍ የምረቃ በዓል

ተረፈ ወርቁ

ኢንጂነር ታደለ ብጡል እስከ ዛሬ ድረስ ፲፬ የሚያህሉ መጻሕፍት ለንባብ አብቅተዋል። እነዚህ መጻሕፍት በአብዛኛዎቹ ደግሞ ስለ ኢትዮጵያ ሀገራችን ታሪክ፣ አኩሪ ባህል፣ ቅርስና የቀድሞ ገናና ሥልጣኔያችንን የሚያወሱ ዘመን አይሽሬ ናቸው። ”The Origin of Humankind” የሚለው የኢትዮጵያን የሺ ዘመናት ታሪክ፣ ገናና ሥልጣኔና የህዝቦቿን ነጻነትና ልዑላዊነት በሰፊው የሚተርከው፣ በፋሽስት ኢጣሊያ ስለተወሰደውና ወደ እናት ምድሩ እንዲመልስም ከፍተኛ የኾነ አስተዋጽኦና ጥረት ስላደረጉበት የአክሱም ሀውልት፣ የዘመናዊት ኢትዮጵያ መሠረት ጣይ ስለሆነው ስለ ዐፄ ቴዎድሮስና ልዑል አለማየሁ ቴዎድሮስ የጻፏቸው የታሪክ መጻሕፍት ይጠቀሳሉ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የዶ/ር መረራ የቡዳ ፖለቲካ እና መቀበል ያቃተው መራራ እውነት

ግርማ ሠይፉ ማሩ

“የኢትዮጵያ የታሪክ ፈተናዎች እና የሚጋጩ ሕልሞች” ዶ/ር መረራ ጉዲና Dr. Merera Gudinas new bookዶ/ር መረራ ጉዲና “የኢትዮጵያ የታሪክ ፈተናዎች እና የሚጋጩ ሕልሞች” በሚል አዲስ መጽሐፍ አስነብቦናል። በአንድ ጋዜጣ ላይ የዶክተር መረራ ከዩኒቨርሲቲ መሰናበት ያመጣው አንድ በጎ ጎን መሆኑን አንብቤያሁ። እኔም በዚህ እስማማለሁ። ብዙ የሀገራችን ፖለቲካኞች ጋዜጠኛ መቅረፀ ድምፅ ይዞ በሚጠይቃቸው ጥያቄ መልስ ከመስጠት የዘለለ ብዕርና ወረቀት አገናኝተው የሚያምኑበትን የፖለቲካ መስመር እና በግላቸው ያላቸውን ምልከታ ማካፈል ይቸግራቸዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የኢትዮጵያውያን ሽግግር - በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር

Ethiopian Transitions: At Home and Abroad (by Kebede Haile) / የኢትዮጵያውያን ሽግግር - በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር (ከበደ ኃይሌ)አዲስ መጽሐፍ በገበያ ላይ ዋለ

የመጽሐፉ ርዕስ፡- Ethiopian Transitions: At Home and Abroad (የኢትዮጵያውያን ሽግግር - በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር)

ፀሐፊ፡- ከበደ ኃይሌ

ቋንቋ፡- እንግሊዝኛ እና አማርኛ

ዋጋ፡- 32.99 የአሜሪካ ዶላር (ጠንካራ ሽፋን)

የገጽ ብዛት፡- 286

አሳታሚ፡- ኦልራይት ፐብሊሺንግ

ገበያ ላይ የዋለው፡- መስከረም 14 ቀን 2008 ዓ.ም. / ኦገስት 24 ቀን 2015 (እ.ኤ.አ.)

ደራሲና ፀሐፊ ከበደ ኃይሌ በቅርቡ እንግሊዝኛ እና በአማርኛ ቋንቋ የጻፉት “Ethiopian Transitions: At Home and Abroad” (የኢትዮጵያውያን ሽግግር - በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር) የተሰኘው መጽሐፍ በቅርቡ በገበያ ላይ መዋሉን ለኢትዮጵያ ዛሬ በላኩት ኢ-ሜይል ገለጡ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በኤርምያስ ለገሠና በዲ/ን ዳንኤል ክብረት በኩል እኛን ማዋራት አሰኘኝ

Daniel Kibret and Ermias Legesseይሄይስ አእምሮ (ከአዲስ አበባ)

ይህ ኢትዮጵያዊነት በስንት ረገድ ቁጭት ውስጥ እየከተተን እንደሆነ እናንተም አስቡት። በእጅጉ የሚገርም ሁኔታ ውስጥ እየከተተን ነው ያለ። በዚህች ሌሊት ሰባት ሰዓት ገደማ ያነበብኩት ጽሑፍ እንኳን ክፉኛ ዕንቅልፍ ነስቶኝ ከሌሊቱ አሥር ሰዓት ላይ ከሚጥመው መኝታየ ተነስቼ ይሄውና መዶግዶግ ያዝኩ - ለነገሩ ሳለ ወያኔ ምን የሚጥም መኝታ አለና!

ሙሉውን አስነብበኝ ...

“የተቆለፈበት ቁልፍ” (መጽሐፍ ግምገማ)

Yetekolefebet qulfኩችዬ

ርዕስ፤ የተቆለፈበት ቁልፍ (439 ገጽ)
ደራሲ፤ ምሕረት ደበበ ገ/ጻዲቅ (ዶ/ር)
ሮሆቦት አታሚዎች፤ አዲስ አበባ፤ መጋቢት 2005

አገር ቤቱ ዳያስፖራ፤ ዳያስፖራው ደግሞ አገር ቤት እየሆነ በመጣበት በዚህ ህልሙም፤ ቅዠቱም፤ ባህሉም፤ ኑሮውም ተወራራሽ በሆነበት ዘመን የሥነ ጥበብ ሰዎች አስጎምዥ የትረካ አውድማ እንደተቸሩ ካወቅኹ ሰንብቻለሁ።

የምሕረት ደበበ ልቦለድ ታሪክ ስድሰት ሺህ ማይል አራርቋቸው በሚኖሩ ያበሻ ሕበረተሰቦች ሁለንተናዊ ባሕርይና ዕጣ-ፈንታ ላይ የተመሠረተ ነው። የደራሲው አንድ እግር አሜሪካ፤ ሌላኛው እግር ደግሞ ኢትዮጵያ መሆን የሁለቱንም ሕብረተሰቦች ውጫዊና ሥነ-ዓዕምሮዋዊ ባሕርይ፤ እንዲሁም የየቤቱን ውሎና ከራሞ በቅርብ ለማስተዋል ዕድል እንደሰጠው ከትርካዎቹ ማስተዋል ይቻላል። ሁለቱም ሕብረተቦች ውስጥ እየተከሰተ ያለው ፈጣንና አንዳንዴም አስፈሪ የሆነ ማኅበራዊ ለውጥ የብዙ ደራሲያንን እንዲሁም በየሙያ ዘርፉ ያሉ ጠቢባንን የሰላ አዕምሮና ብዕር የሚጋብዝ ነውና እንደ ምሕረት ደበበ ያሉ ብዕር ሲያነሱ ደስ ይላል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኤርሚያስ ለገሰ፦ ለጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ

በቅድሚያ መጽሓፉን ጊዜ ሰጥተህ በማንበብ አስደማሚ ምልከታ በመስጠትህ ከልብ አመሰግናለሁ ። የተጻፈበትም አንዱ አላማ ይህ ስለሆነ። ይህ እንደተጠበቀ ሆኖ በእይታህ ላይ እነዚህ ጉድለት ይታይባቸዋል ብለህ ያነሳኸው እና የወደፊት ግምቶችህ ላይ የተወሰነ አስተያየት ለመስጠት የሚጋብዙ ስለሆነ ትንሽ ማለት ፈለኩ። በዚህ አጋጣሚ ሌሎች በመጵሀፉ ይዘት ላይ ዝርዝር ግምገማ ላደረጉ ሰዎች ምስጋናዬ ይድረሳችሁ። ለእያንዳንዱ አስተያየት መስጠት ከጊዜ አኳያ በጣም አስቸጋሪ ስለሆነ የማልዘልቅበትን መንገድ ልጀምረው አልፈለኩም።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የኮብላዩ ሚኒስትር ወጎች

ተመስገን ደሳለኝ

በዚህ ተጠየቅ ጨርፈን የምንመለከተው በኮሙኑዮኬሽን ጽ/ቤት ሚኒስትር ዴኤታ የነበረውና ዛሬ በስደት የሚገኘው የአቶ ኤርሚያስ ለገሰን “የመለስ ትሩፋቶች፣ ባለቤት አልባ ከተማ” የተሰኘው መጽሐፍን ነው። የመድብሉ ጻሐፊ ኤርሚያስን በግል አላውቀውም፤ ለመጀመሪያ ጊዜ በአካል ያየሁት አቶ በረከት ስምዖን እርሱን እና ሽመልስ ከማልን ምክትሎቹ አድርጐ በሚኒስቴር ዲኤታ ማዕረግ መሾሙን በግዮን ሆቴል ለጋዜጠኞች ይፋ ባደረገበት ዝግጅት ላይ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ