ምስጢሩ The Secretክፍል ሰባት
ወለላዬ ከስዊድን
የጤንነት ምስጢር
ማንም ሕመምተኛ የወሰደው ኪኒን
ያድነኛል ብሎ ከቻለ ለማመን
ስላስተላለፈ ለአዕምሮው መልዕክት
በርግጥም ይችላል ጥሩ ፈውስ ማግኘት


በሰውነትህ ውስጥ ሕመም የሚኖረው
በሽታውን ትኩረት ስትሰጠው ብቻ ነው
የጤና መዛባት ስሜት ከተሰማህ
ሕመሙን አታስፋ ለሰዎች ተናግረህ


ሰዎች ስለሕመም ሲያወሩ ማዳመጥ
መንገዱን መክፈት ነው እንዲባባስ ይበልጥ
ሕመማቸው ጸንቶ ቢወተውቱ እንኳን
በመልካም ነገሮች ለውጠህ ወሬውን
ባነጋገር ብቃት ትችላለህ ማዳን


የአዕምሮ ፈጠራን የአርጅቻለሁ እምነት
ከራስህ መንጭቀህ ይገባሃል ማውጣት
ወጣት ነኝ አሁንም ብለህ በማተኮር
ደስታን ጤናን ይዘኽ ትችላለህ መኖር
ስለዚህ አረጀሁ ብለህ በመጨነቅ
ሕመም እያወራህ ዕድሜህን ከመስረቅ
ራስህ ራስህን በዚህ ዘዴ ጠብቅ


መልዕክትና አስተያየት ካለዎ፣ This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it. 
ማስታወሻ ለአንባብያን/ት፦ "The Secret" በሚል ርዕስ አውስትራሊያዊቷ ሮዳ ቢየርን ጽፋው፣ ጋሻው አባተ "ምስጢሩ" በማለት ወደ አማርኛ የመለሰውን መጽሐፍ ገጣሚ ወለላዬ የእያንዳንዱን ምዕራፍ ጭብጥ በግጥም እያስነበበን ይገኛል። ይኽ በመጽሐፉ ካሉት አስር ምዕራፎች ውስጥ ሰባተኛው ነው። መጽሐፍን አንብቦ እጥር ምጥን ባሉ ስንኞች በግጥም ማስቀመጥ በኢትዮጵያ ሥነ-ጽሑፍ ውስጥ ያልተለመደ ሥራ ነው። ምናልባትም ወለላዬ የመጀመሪያው ነው የሚል እምነት አለን።
የኢትዮጵያ ዛሬ ዝግጅት ክፍል

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ