የህይወቴ ታሪክ - ከፊታውራሪ ተክለሃዋርያት ተክለማሪያም

ቅኝት በመስፍን ማሞ (ክፍል ሁለት)  
 
አንባቢ ሆይ በእንደኛው ክፍል የፊታውራሪ ተክለሃዋሪያት ኦቶባዮግራፊ ቅንታችን ከሳያደብር የተነሳው ታዳጊ በእንደምን ያለ ሁኔታ አዲስ አበባን ረግጦ፤ ሀረር አድጎ፤ አደዋ ዘምቶ፤ ሰነባብቶም ውቅያኖስ አቋርጦ፤ አድማስ ዘልቆ፤ ሩሲያ እንደኖረና በትምህርት ዳብሮ፤ በአስተሳሰቡ በልጽጎ ወደ ሀገሩ ኢትዮጵያ እንደተመለሰ ተመልክተናል። ሁለተኛውንና ማሳረጊያውን ክፍል ሁለት ደግሞ እነሆኝ ብለናልና አብረን እናዝግም…
ሙሉውን አስነብበኝ ...

ጃኬት አስወላቂው ጠቅላይ ሚኒስትራችን

እስክንድር ነጋ (አዲስ አበባ)

ሰሞኑን፣ አንድ ግሩም መፅሐፍ እያነበብኹኝ ነው፡፡ ባለፈው አርብ ነው የወጣው፡፡ በዳንኤል ተፈራ የተፃፈና በዶ/ ነጋሳ ጊዳዳ ሕይወት ዙሪያ የሚያጠነጥን ነው፡፡ ብዙ አዳዲስ ነገሮችን ይዟል፡፡ አንድ ስሜቴን የኮረኮረውን ነገር ላካፍላችኹ ወድጃለኹ፡፡

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የአትላንታው ሙቀት!

ክንፉ አሰፋ 

ጁላይ 1፣ አርብ ምሽት አትላንታ ጆርጂያ አውሮፕላን ማረፊያ እንደደረስኩ እንደቅድሞው ብዙ አበሻ ሲርመሰመስ አላየሁም። የአበሻው ትርምስ በ2005 አትላንታ ላይ ተመሳሳይ ፌስቲቫል በተዘጋጀ ግዜ ከነበረው እጅግ ቀዝቀዝ ብሎ ነበር። ይልቁንም ዝግጅቱ አልቆ አትላንታን ስንስነባበት አውሮፕላን ማረፍያው በአበሻ ተጨናንቆ አሜሪካ ሳይሆን፡ ኢትዮጵያ ውስጥ ያለን ነበር የሚመስለው። ሙሉውን አስነብበኝ ...

ለህዝብ መሞት ክብር ነው!

እስክንድር ነጋ (አዲስ አበባ)

ዛሬ፣ ማክሰኞ፣ ሐምሌ 5 2ዐዐ3 አዲስ አበባ ውስጥ ከሚታተመው አዲስ ወሬ ጋዜጣ ጋር አጭር ቃለምልልስ አድርጌያለኹ። የጋዜጣው ማኔጂንግ ኤዲተር፣ ዳንኤል ኃይሉ፣ ባለፈው ሰሞን ከመንገድ ላይ ታፍኖ ተደብድቧል፣ ቢሮው ተፈትሿል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

“ሌባው” ዳኛ እና አሸባሪው አዋጅ

ሲሳይ አጌና
 
ግንቦት ሰባት፣ኦነግ እና ኦብነግ ከድንበር ዘለሎቹ አልቃይዳ እና አልሻባብ ጋር በአሸባሪነት በተፈረጁ በሳምንት ግዜ ውስጥ ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ እና መምህርት ርዕዮት አለሙ ታሰሩ፤በአሸባሪነትም ተከሰሱ፤ወን ላቸውም በስልክ እና በኤሌክትሪክ መስመሮች ላይ ከደረሰ ጉዳት ጋር መያያዙ 15 ዓመታት ወደሁዋላ ወሰደኝ፤ይህ ወቅት እኔ እስር ቤት የነበርኩበት፣የዛሬው የጋዜጠኞቹ ወንጃይ እና ሚንስትር ዴኤታ አቶ ሽመልስ ከማል በአቶ መለስ ዜናዊ ሌባ ዳኛ ተብሎ የተባረረበት፤ይህም ብቻ አይደለም ዛሬ በሽብር የተፈረ ው የስልክ ገመዶች መቁረጥም የተጧጧፈበት ግዜ ነበር።

ብዕርን በማፈን ማንነትን መግደል አይቻልም! አስራደው (ከፈረንሳይ)

ብዕር እስትንፋስ ናት፤ ብዕር ሕይወት ናት፤ ብዕር በሥጋ ወደሙ ላይ ሕይወትን ዕፍ በማለት ሥጋን ነፍስ የምትዘራ ከዕውቀት ዛፍ የምትገኝ ፍሬ ናት፤ ያቺን ፍሬ የቀመሰ ሁለ ማንነቱን አውቋልና ያለ እሷ መኖር አይቻለውም፤ እሷን ያጣ ለት በጨለማ ይከበባል፤ የጨለማ ሕይወት ለመኖር ሲል እስከ ሕይወት መስዋዕትነት ድረስ ዋጋ ይከፍላል፤ ከራሱ አልፎ ድንበር ሳይገድበው፤ ቀለም ሳይለየው፤ የዘር ሃረግ ሳይጠልፈው፤ ከአድማስ እስከ አድማስ የነፃነት ጮራ ለመላው የሰው ልጅ ፍንጥቅ እንዲል  ያደርጋል። (ሙሉውን ጽሁፍ ለማንበብ ይህንን ይጫኑ) 

“የሕይወቴ ታሪክ” ፈታውራሪ ተክለሃዋርያት - ቅኝት በመስፍን ማሞ

የፊታውራሪ ተክለሃዋሪያት ተክለማርያምን የሕይወቴ ታሪክ (ኦቶግራፊ) እንደ ክሽን ልብ አንጠልጣይ ልቦለድ ድርሰት እረፍት እየነሳኝ አነበብኩት። እና ምን ተሰማኝ? የፊታውራሪ ታሪክ አኮራኝ፤ ደግሞም ውስጤን አብሰለሰለኝ፤ ከሁሉም በላይ ግን አስተማረኝ። (ሙሉውን ጽሁፍ ለማንበብ ይህንን ይጫኑ)

«ከጅምሩ የተበላሸ ነው» ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ

  እስክንድር ነጋ (አዲስ አበባ) 

 ባለፈው ሳምንት እንዳይታተም ከተከለከለው መፅሐፋችን (ፀሐፊዎቹ እኔና ሠርክዓለም ፋሲል ነን) የተወሰነ ቀንጭቤ ማቅረቤ ይታወሳል። የተቀነጨበው ፅሑፍ የሚተነትነው በምርጫ 97 ሳቢያ የተጨፈጨፉትን ንፁሃን ዜጐች ጉዳይ እንዲመረምር በፓርላማ ተቋቁሞ የነበረው አጣሪ ኮሚሽን፣ በወህኒ ቤት ተገኝቶ የቅንጅት አመራሮችንና ጋዜጠኞችን ያነጋገረበትን ታሪካዊ ስብሰባ ነው።

 

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አባ ጳውሎስና አባ ገ/መድህን ሲገመገሙ (ከዳዊት አዘነ)

በገጽ 96 ላይ ከሰው ጋር ተስማምተው ስራ መስራት ስላልቻሉ በነጻ ቀለብ እየተሰፈረላቸው ሲኖሩ ስኮላር ሽፕ ያገኛሉ። ከዚያም ወደ ድርግ ጽ/ቤት ሄደው ቤተ ክህነት ስለተጣላኝ አይሰደኝምና እናንተው ስደዱኝ ብለው ደርጎችን ይማጸናሉ። ከዚአም ደርግ ሰውየው ለትምህርት ዲሄዱ ትቃወማላችሁ እንዴ? ብሎ ቤተ ክህነትን ይጠይቃል። ቤተ ክህነትም እንደማትቃወም ታስታውቃለች። ከዚያም የመጓጓዣ ተከፍሎላቸው፤ የመንገደኛ ወጭ የኪስ ገንዘብ ተከፍሏቸውና ደብዳቤ ተጽፎላቸው በክብር ነው የወጡት ይላል መጽሀፉ። (ሙሉውን ጽሁፍ ለማንበብ ይህንን ይጫኑ)