ድንቄም የአዲስ አበባ ማስተር ፕላን? ማስተር ፕላኑማ የዘ-ህወሓት ነው!

ፕ/ር አለማየሁ ገብረማርያም (ትርጉም:- ነጻነት ለሀገሬ)

TPLF's Addis Ababa master plan

የጸሐፊው ማስታወሻ፡ መለያ ምልክት ምንድን ነው? ደህና፣ “በስም ውስጥ ያለው ምንድን ነው? ያ ጽጌረዳ እያልን የምንጠራው/በሌላ በማንኛውም ስም ቢጠራም ያው ጣፋጭ ሽታው መሽተቱ አይቀርም…“ ብሎ ነበር ሸክስፒር። “ካራቱሪ እና የሕንድ ኃያልነት በኢትዮጵያ” በሚል ርዕስ በቅርቡ ባቀረብኩት ጽሑፍ በካራቱሪ ዓለም አቀፍ ከኢትዮጵያ በተነጠቀው መሬት ላይ የበቀሉት ጽጌረዳዎች በእርግጥ ጽጌረዳዎች አይደሉም የሚለው እውነት ሊሆን ይችላል። ይህ በኢትዮጵያ የመሬት ነጠቃ እና ዘረፋ እያካሄድኩት ያለው ጽሑፍ ለሶስተኛው ጊዜ ያዘጋጀሁት ትችቴ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የአቶ ግርማ ካሳ "ቅዠት"

ስንታየሁ በሱፈቃድ

የተወሰኑ ድረ ገጾችን አለፍ አልፍ እያልኩ ባነብም ልምድ ማጣቱ ይሁን የግዜ እጥረቱ ለእኔም ግልጽ ባልሆነ ምክንያት መጻፉ አይሆንልኝም። አንዳንድ ጽሁፎች እየገፋፉኝ ለመጻፍ ብሞክርም ተሳክቶልኝ ለንባብ ማብቃት አልቻልኩም።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የላላው ጭቃ

የላላው ጭቃአንዱዓለም ተፈራ

አሁንም ቀኑን እንቆጥራለን። ሌሊቱንም እንዲሁ። አሁንም የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባርን ተግባር እንዘረዝራለን። አሁንም ሰዎች በገዛ ሀገራቸው እንዳውሬ እየታደኑ፣ እየተያዙ፣ ይታሰራሉ፣ ከሀገር ይሰደዳሉ፣ ይገደላሉ፣ ... እንላለን። አሁንም በየቤተክርስትያኑና በየመስጂዱ እግዚዖ እንላለን። አሁንም የሀገራችን ለም መሬት ከባለቤቱ ኢትዮጵያዊ እየተነጠቀ፤ ለሹማምንትና ለውጪ ሀገር ባለሀብቶች ተሠጠ እያልን እናላዝናለን። አሁንም ሹማምንት ጀኔራሎችና ዘመዶቻቸው፤ ከተማዎችን ፎቅ በፎቅ አድርገው፤ ድሃን ማደሪያ አሣጡት እንላለን። ምን የማንለው አለ! ብቻ በገባንበት አረንቋ አሁንም እንረግጣለን።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አሁን ለእነ ዶ/ር ብርሃኑ የምጠይቀው

ግርማ ካሳ

Dr Berhanu Nega. ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ

አንዳንንድ ወገኖች በግንቦት ሰባቶች ላይ የግል ችግር ያለብኝ ይመስላቸዋል። አይደለም። ከነርሱ ጋር የዓላማ ልዩነት የለኝም። ልዩነቴ የስትራቴጂ ነው። ግንቦት ሰባት ውስጥ ያሉ ወገኖች ዳይናሚክ የሆኑ ትልቅ ፖቴንሻል ያላቸው እንደሆነ አውቃለሁ። ሊቀመንበሩ ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ፣ በቅንጅት ጊዜ ቁልፍ ሚና የተጫወቱ መሪ ናቸው። ብዙዎቻችንን ኢንስፓየር ያደረጉ። ሆኖም በግንቦት ሰባት አመራርነት የወሰዱት ስትራቴጂ ግን ያላቸውን ፖቴንሻል እንዲጠቀሙበት የረዳቸው አይመስለኝም።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አንዳርጋቸው በምናቤ

ተስፋዬ ገብረአብ

Andargachew Tsege. አንዳርጋቸው ፅጌ

እነሆ! ቅዳሜ ዞሮ መጣ። በዚህች የቅዳሜ ምሽት ስለ አንዳርጋቸው ጥቂት አወጋ ዘንድ መንፈሴ መራኝ። አዲስ ነገር አትጠብቁ። ከቀንዱም ከሸኾናውም ዝም ብዬ አወጋለሁ። የምትሠሩት ሌላ አስቸኳይ ጉዳይ ካላችሁ ይህን ጽሑፍ ለማንበብ ጊዜአችሁን አታቃጥሉ። እንደው ዘና ብላችሁ ከሆነ ግን ብታነቡት ምንም አይላችሁም።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

እውን ወልቃይት ትግሬ ነው?

ይገረም አለሙ

Goonder before and after 1991

ወቅቱ 1994 ክረምት ነው። በየዓመቱ ትምህርት ቤቶች ሲዘጉ መምህራንን አንድም በአብዮታዊ ዴሞክራሲ ለማጥመቅ ሁለትም ሥራ ፈተው ከዋሉ የሚሠሩት ስለማይታወቅ ጠርንፎ ለማቆየት የሚዘጋጀው ስብሰባ ጎጃም ደብረ ማርቆስ በሦስት አዳራሾች እየተካሄደ ነው። ቤተ መንግሥት አዳራሽ፣ ሲኒማ ቤትና መንገድ ትራንስፖርት አዳራሽ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ምላሽ ለተስፋዬ ገብረአብ፤ "የአባይ ፀሐዬ ጦርነት" በሚለው ላይ

ግርማ ካሳ

Tesfaye Gebreab, ተስፋዬ ገብረአብ

አቶ ተስፋዬ ገብረአብ በአንድ ወቅት የኢሕአዴግ ባለሥልጣን የነበሩ ሰው ናቸው። ጥሩ ፀሐፊ ናቸው። ከኦሮሞ ብሔረተኞች ጋር የቅርብ ግንኙነት አላቸው። አንድ ወቅት እንደውም የኦሮሞ ተማሪዎች ማኅህበር ላይ የክብር እንግዳ ሆኖ ቀርበው ነበር። በዚያን ወቅት “በሞጋሳ እኔም ኦሮሞ ነኝ” ብለው ነበር። ሞጋሳ አንድ ሰው “ኦሮሞ” ባይሆንም የኦሮሞን ባህልንና ቋንቋን ከተቀበለ፣ በኦሮሞ “ሽማግሌዎች” ፍቃድ “ኦሮሞ” የሚሆንብት ሥርዓት ነው (naturalized ኦሮሞነት)።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የአባይ ፀሐዬ ጦርነት

ተስፋዬ ገብረአብ (Gadaa)

Abay Tsehaye. አባይ ፀሐዬ

ከኦሮሚያ አመጽ ጋር በተያያዘ አባይ ፀሐዬ ስሙ በተደጋጋሚ ይነሳል። አንዳንድ ደንፊ ንግግሮች መናገሩንም ስናነብ ሰነባብተናል። ምን እንደነካው እንጃ እንጂ ጠባዩ እንኳ እንዲያ አልነበረም። አባይ በጠባዩ ድመት መሆኑ ነበር የሚታወቀው። ሊያጠቃ ሲፈልግ እንደ ፈረስ ጋማህን እያሻሸ እንጂ እንደ ቋረኛው ካሳ ጎራዴ አያወዛውዝም። ከታላቁ የኦሮሚያ አመጽ ጋር በተያያዘ “በሚናገራቸው ንግግሮች” ግን ስሜቱን መቆጣጠር የተቸገረ ይመስላል። ዞረም ቀረ አባይ ፀሐዬ እና ጓደኞቹ የገጠማቸውን ጦርነት በአሸናፊነት ለመወጣት መጣራቸውን ቀጥለዋል። ይሳካላቸው ይሆን?

ሙሉውን አስነብበኝ ...

“የቡዳ ፖለቲካ” ዶ/ር መረራ እና አቶ ግርማ

ይገረም አለሙ

Dr. Merera Gudan and Girma Seifu. ዶ/ር መረራ ጉዲና (በግራ) እና አቶ ግርማ ሰይፉ (በቀኝ)

ለዚህች ጽሑፍ መነሻ ምክንያት የሆነኝ አቶ ግርማ ሰይፉ “የዶ/ር መረራ የቡዳ ፖለቲካ እና መቀበል ያቃተው መራራ እውነት”በሚል ርዕስ ያስነበቡን ጽሑፍ ሲሆን፤ ርሳቸው ለጽሑፋቸው ምክንያት የሆናቸው ደግሞ “የኢትዮጵያ የታሪክ ፈተናዎች እና የሚጋጩ ሕልሞች” የሚለው የዶ/ር መረራ መጽሐፍ እንደሆነ ገልጸዋል። የቡዳ ፖለቲካ የሚለው ቃልም ከዚሁ መጽሐፍ የተገኘ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

መተባበር በተግባር

Ethiopia Oromo students protest addis ababa plan. የኦሮሞ ተማሪዎች በአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ላይ ያሰሙት ተቃውሞይገረም አለሙ

በሀገር ውስጥም በውጪም ቁጥራው እጅግ የበዛ ተግባራቸው ግን ብዙም የማይታይ ፓርቲዎች አሉ። እነዚህ የሚችሉት ተዋህደው አንድ በመሆን፤ የማይችሉት ተባብረው ትብብርም ይሁን ግንባር በመፍጠር የነጻነት ቀናችንን ለማፋጠን የሚያስችል ትግል ያደርጉ ዘንድ ስንመኝ፣ ስንጠይቅ፣ ስንማጸን፣ ይህን ባለማድረጋቸውም ስንኮንን ወዘተ ዓመታት ተቆጥረዋል። እነርሱ ግን መተባበሩ ቀርቶ መከባበሩ አልሆን ብሎአቸው፣ ተደጋግፎ መቆሙ ቢቀር አንዱ ለአንዱ እንቅፋት ከመሆን መቆጠብ ተስኖአቸው ወያኔ ያሻውን እንዳሻውና ባሰኘው መንገድና ግዜ እየፈጸመ ከዚህ እንዲደርስ አድርገውታል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ