ከኦሮሞ ማዕበል ማግስት …

ተስፋዬ ገብረአብ

በዓለማችን ላይ ወጣቶች በአንድ ልብ የተሳተፉበት ያልተሳካ የአብዮት ታሪክ አናውቅም። የጊዜ ጉዳይ ብቻ ነው። ይህችን እየፃፍኩ ሳለ የማያቋርጥ፣ የተቀናጀ የአመፅ ዜና ከኢትዮ-ኦሮሚያ እየሰማሁ ነበር። ዝምታው ማብቃቱ ግልፅ ነበር። የኦሮሚያ ወጣቶች የሥርዓቱን ታጣቂ ኃይል በጦርና በጠመንጃ ይፋለሙት ይዘዋል። ከሻሸመኔ ወደ አዲስ አበባ መንገድ ተዘግቶአል። ልማደኛዋ ኮፈሌ ጦር ሜዳ ሆናለች። ብረት ለበስ ጦር ኮፈሌና ሻሸመኔ ገብቷል። በጥቅሉ ወለጋና ሐረርጌ ፀጥታ የለም። ሱሉልታ ብሶበታል። ጭራሽ ገበሬዎቹ ያስለቀቁትን መሬት መከፋፈል ጀምረዋል። ደራ ነፃ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በዚህ ሁኔታ ኢትዮጵያ እንደ ሀገር ትቀጥል ይሆን?

ግርማ ካሳ

የምታዩት ፎቶ ምን ያህል በኦሮሚያ ያለው እንቅስቃሴ በአክራሪዎች፣ በኦነጋውያን እንደተጠለፈ የሚያሳይ ነው

ከ25 ዓመታት በፊት ህወሓት/ኢህአዴግ ከፋፍሎ ለመግዛት በሚል የዘረጋው የዘር ፖለቲካ ወይንም የነርሱን አባባል ልጠቀምና “የብሔር ብሔረሰቦች” ፖለቲካ፣ ብዙዎች ኢትዮጵያን እንደ ሀገር ሊያጠፋ የሚችል ትልቅ አደጋ “time bomb” እንደሚሆን ሲያስጠነቅቁ ነበር።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የብአዴን እና የኦህዴድ አገልጋይነት እስክምን ድረስ

ይገረም አለሙ

ወያኔ ብአዴንና ኦህዴድ የሚባሉ አገልጋዮቸን ፈጥሮ፣ ኢትዮጵያውያንን በጎሣ አከፋፍሎና ለአገዛዙ እንዲመቸው አድርጎ አደላድሎ ለ17 ዓመታት የተዋጋለትን ዓላማውን ተግባራዊ ከማድረግ አልፎ ሃያ አራት ዓመታት በሥልጣን መቆየት በመቻሉ ሊደነቅ ይገባል። ለዴሞክራሲ እንታገላለን የሚሉ እንደ ወፍ ዘራሽ በየቦታው በቅለው ሳይለያዩ ተለያይተው፣ ሳይነጋገሩ ተጣልተው፣ የቃላት እንጂ የተግባር ሰውነት ርቆአቸው ሃያ አምስት ዓመታት ስንዝር መራመድ ባልቻሉበት ወያኔ እኩይ ዓላማውን ለማሳካት አንድነቱን አጥብቆ፣ ገመናውን ደብቆ በሌሎችም ተጠቅሞ መዝለቅ መቻሉን ማድነቅ አለመቻል የራስን ድክመት ለመቀበል አለመፍቀድ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የሁሉም ጠላት ወያኔ ነው!

ወያኔ የኦሮሞ ጠላት ነው

አንተነህ መርዕድ

Abayi Tsehaye አባይ ፀሐዬ

መለስ ሲያጉረመርምበት ብርክ የሚይዘውና የሚሙለጨለጨው፣ ጓደኞቹን ደጋግሞ በፍርሃቱ የሸጠው አባይ ፀሃዬ ዞር ዞር ብሎ ሲመለከት ከሱ የተሻሉና የሚያስፈሩት ህወሃቶች የሌሉ መሆናቸውን በማረጋገጡ በየመድረኩ ብቅ እያለ መፎከርና መዘባረቅ የእለት ተእለት ሥራው ሆኗል። በተለይም በዋና ባለቤትነት የአዲስ አበባን መሬት ሸጦ ከጨረሰ በኋላ የአካባቢውን ገበሬዎች ከነመሬታቸው ሊቀራመት ያደባበት ተንኮል አልሠራ ሲል “ልክ እናስገባቸዋለን” ሲል ፎከረ። አሁን ደግሞ ፉከራው የለኮሰውን እሳት ማዳፈን ተስኖት “ወያኔ የኦሮሞ ጠላት አይደለም” የሚል የሽሽት ሽምጥ ሩጫ ይዟል። እሳቱ ግን እሱን ሳይለበልበው የሚመለስ አይደለም።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ካልተስማማን እንደሀገር እንጠፋለን

ግርማ ካሳ

በግምት ከሃያ አራት ዓመታት በፊት ይሆናል ቀኑ። በኢትዮጵያ እርቅና ሰላም እንዲኖር ብዙ ጊዜ የሚደክሙና የሚጸልዩ፣ ቄስ ቶሎሳ ጉዲና የሚባሉ አንድ መንፈሳዊ አባት፣ ምዕመናንን ሲያስተምሩ የተናገሩት፣ ሁልጊዜ የማስታወሰውና የማልረሳው አባባል ነበር።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ማንነት መሬት ላይ አይዘራም

ጌታቸው ኃይሌ

Identity crisis ማነኝ?

ባለፉት ጥቂት ሳምንታት ማንነት ዋና የመወያያ ርዕስ ሆኖ ቈይቷል። የሥነ ልቡና ምሁራን identity crisis የሚሉት ነው እንዳልል ያተኰረው "እኔ ማነኝ" ከሚለው ላይ አይደለም። ያተኮረው "ማንነት ከመሬት ጋር ይያያዛል ወይስ አይያያዝም?" ከሚለው ጥያቄ ላይ ነው። ውይይቱን እንዳዳመጥኩትና እንደሰማሁት፣ እኔም አስተያየቴን እንድሰጥ ተጠይቄ እንደተቸሁት፣ ማንነትን ከመሬት ጋር የሚያያይዙ እምነታቸውን ከኃይማኖት እምነት ደረጃ አድርሰውታል። ስለዚህ እነሱን በማስረጃ ማሳመን ሃይማኖታችሁን ለውጡ እንደማለት ሆኗል። "እምነቱ ሀገር አጥፊ ነው፤ ተውት" ቢባሉም፣ ማንነታቸው ከያዙት መሬት ጋር ከተቆራኘ፣ ይህ አደገኛ አቋማቸው ለሚያስከትለው ሀገራዊ ችግር አንዳች ሥጋት አይታይባቸውም። ክልል ይዞ ኢትዮጵያዊ መሆን ይቻላል የሚሉም አይጠፉም። መሳሳታቸውን መስማት አይፈልጉም፤ ግን ማንነት የሚዘራበት መሬት የሚያስፈልገው ዳጉሳ አይደለም።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ለልጅ የሳቁለት፣ ለውሻ የሮጡለት፣ ለፖለቲከኛ ያጨበጨቡለት

ይገረም አለሙ

የአበው ተረት ለልጅ የሳቁለት ለውሻ የሮጡለት ነው የሚለው። ለፖለቲከኛ ያጨበጨቡለት የሚል ቢጨመርበት ተስማሚ ይመስለኛል። ልጅ ከሳቁለት ሁሉ ቦታ እየገባ ነገር ያበላሻል፤ ውሻ ከሮጡለት ጥሎ ካላንደባለለ ወይ ካልቦጨቀ አይመለስም ፖለቲከኛም ካጨበጨቡለት አበው ልቤ አደገና ያለ ቁመቴ አላስገባ አለኝ የገዛ ቤቴ እንደሚሉት ይሆንና ከእኔ በላይ ለአሳር በሚል መታበይ ብዙ ጥፋት ያደርሳል ኋላም ራሱን ያዋርዳል። እኛም ጥሎብን ይሁን ባህል ሆኖብን ባይታወቅም እየኮተኮቱ ማሰደግ እየገሩ ለወግ ማዕረግ ከማብቃት ይልቅ እያሞካሹ ማበላሹትን እያጨበጨቡ ወደ ገድል መግፋቱን ተክነንበታል። በዚህ መንገድ ስንት ለሀገርና ለወገን ሊጠቅሙ ይችሉ የነበሩ ሰዎችን አጥተናል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የመሳይ ከበደ በር

ተስፋዬ ገብረአብ

ዛሬ ላይ ቆመው ነገን ለማወቅ የሚችሉ ሰዎች “ነቢይ” ሲባሉ ኖረዋል። በዘመናችን ቋንቋ “የፖለቲካ ተንታኝ” ማለት ይሆን? ይህን የሚገልፅ አንድ አባባል አውቃለሁ፣ “ትናንት ታሪክ ሆኖአል፤ ዛሬ ስጦታ ነው፤ ነገ ደግሞ ምስጢር”

ሙሉውን አስነብበኝ ...

መልስ ለአቶ ብርሃነመስቀል የ”ኦሮሞ ሕዝብ ጥያቄዎች” ባሉት ላይ

ግርማ ካሳ

አቶ ብርሃነመስቀል አበበ፣ በኦሮሞ ብሔረሰብ መብት ዙሪያ በተለያዩ ጊዜያት የተለያዩ ጽሁፎችን ይጽፋሉ። ቢቢሲ በአፋን ኦሮሞ ቋንቋ ስርጭት እንዲኖረው ፔቲሽኖችን በማስፍረም አንድ ዘመቻ እንደነበረ የምናስታወሰው ነው። ይሄንን ዘመቻ ይመሩ ከነበሩት መካከል አቶ ብርሃነመስቀል አንዱ ነበሩ። እኔም ሆንኩም በርካታ ኢትዮጵያዊያን ፔቲሽኑ ላይ ፊርማችንን በማስፈር፣ ፔቲሽኑ ያልፈረሙ እንዲፈረሙ በማበረታታት እንደነ አቶ ብርሃነመስቀል ባይሆንም፣ የድርሻችንን አበርክተናል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የኦሮሞ ሕዝብ ሕገ መንግሥታዊ የመብት ጥያቄዎች ለድርድር እና ለልመና የሚቀርቡ አይደሉም

ብርሃነመስቀል አበበ

አንዳንድ ወዳጆቼ የኢትዮጵያ መንግሥት የኦሮሞ ሕዝብ እየጠየቀ ላለው፣

1ኛ፣ በጉልበት እና ሕግን ሽፋን በማድርግ የተዘረፈው የኦሮሞ ሕዝብ መሬት እንድመለስ፣ የወረራው መሠረት የሆኑት ሕጎች እንዲሻሩና የዘረፋ ተቐማቶቹ እንዲፈርሱ፣

2ኛ፣ ኦሮምኛ ከአማርኛ ጎን ለጎን የኢትዮጽያ ፌድራል መንግሥት የሥራ ቐንቐ እንዲሆን፣

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ