የአንድነቱን ጉባዔ በወፍ በረር

ዳንኤል ተፈራ 

እንደ መነሻ 

ከሁለት ወር በፊት አንድነትን እንዲመሩ በጠቅላላ ጉባዔ የተመረጡት ኢ/ር ግዛቸው ሺፈራው ጥቅምት ሁለት ቀን 2007 ዓ.ም ካቢኔያቸውን በትነው ስልጣናቸውን በፈቃዳቸው ለብሔራዊ ምክር ቤቱ አስረከቡ፡፡ የቀድሞው ፕሬዘዳንት ኢ/ር ግዛቸው ለምክር ቤቱ ባሰሙት ንግግር በአመራራቸው ያልተደሰቱ በሀገር ውስጥና በውጭ የሚኖሩ የፓርቲው አባላትና ደጋፊዎችን የ‹‹ልቀቅ›› ጫና መቋቋም እንዳልቻሉና ከህሊናቸው ጋር ተማክረው ለፓርቲው ጥቅም ሲባል በፈቃዳቸው ሃላፊነታቸውን ለመልቀቅ እንደወሰኑ ተናገሩ፡፡

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኢትዮጵያ፡ እ.ኤ.አ ኖቬምብር 24/1974ን እናስታውስ

ፕ/ር አለማየሁ ገብረማርያም (ትርጉም:- ነጻነት ለሀገሬ)

ባለፈው ሳምንት በዩናይትድ ስቴትስ አሜሪካ የሚኖሩ በርካታ ኢትዮጵያውያን/ት ቤተሰቦች ከዘመዶቻቸው እና ከጓደኞቻቸው ጋር በመሆን በኢትዮጵያ ታሪክ በመጥፎ ገጽታው ሲታወስ የሚኖረውን እ.ኤ.አ ኖቬምበር 14/1974 በኢትዮጵያውያን ላይ የተፈጸመውን የእልቂት ሰለባዎች ለማስታወስ በአንድ ላይ ተሰባስበው የጸሎት ስርዓት አድርገዋል፡፡ በዚያ የጥላቻ ዕለት የወታደራዊው አምባገነን ስብስብ ተራ ስብሰባ በማድረግ 60 ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣኖችን፣ የመንግስት ሰራተኞችን፣ አርበኞች ከፍተኛ ማዕረግ ያላቸውን ወታደራዊ መኮንኖችን፣ የተማሩ ወታደራዊ ባለስልጣናትን እና የግርማዊ ቀዳማዊ አጼ ኃይለ ስላሴን ልዩ የጥበቃ አባላት ያካተተ የግድያ እልቂት ለመፈጸም ተራ እና አስደንጋጭ ውሳኔን አሳለፈ፡፡

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ማንነት ፍለጋ! (ክፍል 1)

አሰፋ ጫቦ

 

እንዲያው ዘው ተብሎ አይገባ ነገር! ” ቤቶች!” ተብሎ” ደጆች!” ተብሎ “ይግቡ/ግባ!” ተብሎ ነው እንጅ። ጠፍቼ ስነበትኩ።ከርምኩ ሳይሻል አይቀርም።”ለመሆኑ አስፋ ጫቦ የት ገባ” ብለው በአደባባይ ከጠየቁት ወሰንሰገድ ገ/ኪዳንንና እንዳለ ጌታ ከበደን ሌሎች እዚህ በስም ያልጠቀስኳቸዉን ሁሉ አመስግናለሁ።ለክፉም ለደጉም ጠያቂ አያሳጣችህ! እኔማ ሌላ ምን እላለሁ ! የቤት ክህነት አባቶች እንደሚሉት ሱባዔ ገብቼ ነበር።ከዚያው ከቤተክህነት ተውሸ፤(ነበርኩብትምና) “ዘኀሀለፈ ሥርየት ወለዘይመጽዕ እቅበት” እላለሁ። ነጠላ ትርጉሙ “ያለፈው ይሰረዝ ይደለዝ ለመጭው መታቀብን/መቆጠብን  ስጠኝ/ስጠን!” እንደማለት ነው።በምወደው መጽሐፍ Gone with Wind   ስካርሌት ኦሐራ (Scarlet O’Hara) Tomorrow is Another Day ትላለች።። “ነገም ሌላ ቀን ነዉ” ብሎታል ተርጏሚው ነብይ መኮንን።እኔም እንድያ እንዳልኩ ይቆጠርልኝ!

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የእስክንድር ነጋ ያገባኛል ባይነት!

በላይ ማናዬ

‹‹መብቴን አሳልፌ አልሰጥም፤ የትም ብሆን ስለመብቴና ሀገሬ ያገባኛል፡፡ እዚህ ከሚጠይቁኝ ሰዎች ጋር የፈለኩትን ማውራት እችላለሁ፡፡ እናንተ ከፈለጋችሁ በር ላይ መልሷቸው እንጂ እኔ ጋር ከመጡ በኋላ ስለሀገሬ ከእነሱ ጋር መነጋገር መብቴ ነው፡፡ አዎ የትም ቦታ ብሆን፣ መቼም ቢሆን ስለ ሀገሬ ያገባኛል!››

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኢትዮጵያን ለማጥፋት የሚደረግ ደባ

ፕ/ር አለማየሁ ገብረማርያም (ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ)

ለአራት አስርት ዓመታት እራሱን ህዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ (ህወሀት) እያለ የሚጠራው እና በአሁኑ ጊዜ በኢትዮጵያ ህዝብ ጫንቃ ላይ ከህዝብ ፍላጎት ውጭ በኃይል በስልጣን ወንበር ላይ ተፈናጥጦ የሚገኘው የወሮበላ የማፊያ ቡድን ኢትዮጵያን ለማጥፋት ቀጣይነት ያለው እና የማያቋርጥ የፖለቲካ፣ የማህበራዊ እና የባህል ጦርነት በመክፈት ዕቅድ አውጥቶ በመንቀሳቀስ ላይ ይገኛል፡፡

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የነፃነቴ ዋጋ ነብሴ ነው!!!

ግርማ ሰይፉ ማሩ

መረጃ በሃያ አንደኛው ክፍለ ዘመን ጠቃሚ ነው ብሎ መንገር ለቀባሪ እንደማርዳት ነው፡፡ የተሟላ መረጃ የሰውን ልጅ ሙሉ ያደርገዋል፡፡ መረጃን አጣሞ ማቅረብ ደግሞ የሰውን ልጅ ውሳኔ ለማጣመም ካልሆነ በስተቀር ግቡ ምን ሊሆን እንደሚችል አይገባኝም፡፡ በሰሞኑ ሰው በላው የኢትዮጵያ ፖለቲካ በጥርሱም በጥፍሩም ዘመቻ የጀመረው እኔ ላይ ነው፡፡ ዓላማው ግልፅ ነው፡፡ በነፃነት የማሰብ መብቴን ለድርድር እንዳቀርብ ነው፡፡ ለነፃነቴ ያለኝን ዋጋ የማያውቁ ሰዎችን ይህንን ለማድረግ ቢሞክር ካላቸው የመረጃ እጥረት ወይም ማወቅ ባለመፈለጋቸው ነው፡፡

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የመለስ “ትሩፋቶች” (ባለቤት አልባ ከተማ)

ደራሲ:- ኤርምያስ ለገሰ
ቅኝት:- መስፍን ማሞ ተሰማ

መንደርደሪያ
በድሮ ዘመን የኖሩ እንስሳት እንዲህ ዘመሩ።
የእንግሊዝ አራዊት፤
የአየርላንድ አራዊት፤
የየሀገሩ ሁሉ አራዊት፤
ተሳተፉ የደስታዬን ምንጩን፤
ስለመጪው ብሩህ ዘመን!
ይዘገያል ወይ ይፈጥናል፤
ያ! ቀን ግን ይመጣል፤
ጨቋኙ ሰው ይገረሰሳል! . . . ዘምረው ዝም አላሉም። ዘምረው አመፁ። አብዮት አፈነዱ፤ የእንስሳት አብዮት። በሚኖሩበት ሀገር - በእነሱ አጠራር፤ የእርሻ ጣቢያ - ለዘመናት በጭቆና ቀንበር ረግጦ ሲገዛቸውና ሲመዘብራቸው በኖረው የሰው ዘር ገዢያቸውና ግብረ አበሮቹ ላይ ሆ! ብለው ተነሱ። ቀንበር በቃን። ባርነት በቃን። ብዝበዛ በቃን። … ነፃነት እንጂ። 

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ታላቁ ረኃብ፡ ህወሀት አሁንም ቢሆን ለመስረቅ እና ለመዝረፍ ፈቃድ አለው

ፕ/ር አለማየሁ ገብረማርያም (ትርጉም - ነጻነት ለሀገሬ)

እ.ኤ.አ በ1984 የተከሰተው የኢትዮጵያ ታላቁ ረኃብ ሲታወስ (ክፍል 2)
ባለፈው ሳምንት ባቀረብኩት ትችቴ (እ.ኤ.አ በ1984 የተከሰተው የኢትዮጵያ ታላቁ ረኃብ ሲታወስ፡ ክፍል1)፣ ላለፉት በርካታ ዓመታት ረኃብን በማስመልከት ሳቀርባቸው በነበሩት ትችቶች የህዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ እና አሁን በህይወት የሌለው መሪው መለስ ዜናዊ እ.ኤ.አ ከ1991 ጀምሮ በኢትዮጵያ ውስጥ ምንም ዓይነት ረኃብ የለም በማለት ሙልጭ አድርገው በመካድ ሲያደርጉት የነበረውን ተራ ቅጥፈት በማጋለጥ በተጨባጭ መረጃዎች ላይ በመመስረት ስሞግት የቆየሁባቸውን ዋና ዋና ጭብጦች በማካተት ክለሳ ማድረጌ ይታወሳል፡፡

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ዝምታው ለምን ነው? (ጋዜጠኛ አንተነህ መርዕድ)

- ኢትዮጵያ አደገኛ ሁኔታ ውስጥ ነው ያለችው።
- መንግስት እንደድሮው መግዛት ተስኖታል
- ህዝቡም እንደድሮው መገዛት ታክቶታል
- የተቃዋሚው ቋንቋም እንደባቢሎኖች የተከፋፈለበት ወቅት ላይ ነን
- ከዚያም ብሶ ሚድያው ታፍኗል።
ትግሉን በተደራጀ መልክ ዳር የሚያደርስ ጠርቶ ባልወጣበት ሁኔታ ህዝባዊ ዓመጽ ሊፈነዳ ጫፍ ላይ መድረሱን ለማወቅ ሊቅነት የሚጠይቅ አልሆነም። በዚህ ኔታ ዐመጽ ከተነሳም የሚከተለው ትርምስና እልቂት ቀላል ስላይደለ ንፁህ ህሊና ያለው ሁሉ በግልፅ ታይቶት መፍራት አለበት። ይህ ፍርሃት በጎ ፍርሃት ሊሆን የሚችለው ወደ መፍትሄው መሄድ ካስቻለን ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

‹‹እስሬ፣ ጥሩ ክርስቲያን ሰውና ታጋይ አድርጎኛል››

‹‹ኢህአዴግ በጭቆና ውስጥ ጸጥ ብሎ የተቀመጠን ሕዝብ እየቆሰቆሰ ነው››

ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ፣ ከቃሊቲ እስር ቤት

(በኤሊያስ ገብሩ – ጋዜጠኛ)
ትናንት፣ በዕለተ ዓርብ እኔ እና የዕንቁ መጽሄት ማኔጂንግ ዳይሬክተር ከሆነው ፍቃዱ ማህተመወርቅ (ባሪያው) ጋር ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋንና ፖለቲከኛን አቶ አንዷለም አራጌን በቃሊቲ ተገኝተን ጠይቀናቸው ነበር፡፡

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ